Wednesday, May 16, 2012

ትዝታ ወ ግንቦት ሰባት! (አቤ ቶኪቻው)

አቤ ቶኪቻው | May 16th, 2012 at 4:16 am | |
ሰላም ወዳጄ… በቀጠሯችን መሰረት መጥቻለሁ።
ትላንት ግንቦት ሰባት ነበር። ይቺ ቀን ለኛ የተለየች ቀን ነች። የዲሞክራሲ መብራት ብልጭ ብላ የጠፋችበት በርሱ ጦስም በርካታ አቅም እና ችሎታ ያላቸው ትራንስፎረመሮች ተቃጥለው፤ በምትካቸው ትራንስፎርሜሽን የተባለ ቃል መተካት የጀመረባት ታሪካዊ ቀን። እስቲ ያቺን ሰዓት ትንሽ እንዘክራት…
አንድ
እኔ በምርጫ ዘጠና ሰባት ጎጃም አካባቢ ነበርኩ። የአቤ ጎበኛው የትውልድ ቦታ የሆነችው አቸፈር፣ ዱር ቤቴ፤ እንዲሁም አዴት እና መራዊ ከዛም አልፎ ሶስት እና አራት ሰዓት በእግር የሚያስገቡ ገጠራ ገጠሮችን በስራዬ ሰበብ ሳስሳቸው ነበር። ከዛ አካባቢ በአንዱ ገጠር የሚከተለውን አንዱ አጫወተኝ።
“ይገርምሃል ጋሼ ሪም ቀበሌ ህዝብ ተጨንቋል።”
“ምን አጋጠመው?”
“የቀበሌው ሰው ሁሉ ካርዱን ለቅንጅት ሊሰጥ ተስማመቶ ነበር።”
“ታድያስ?”
“ኋላ ላይ ሲቆጠር አንድ ካርድ ለንቢቱ ገብታ ተገኘች።”
“ይገርማል። ታድያ ጭንቀቱ ከምን መጣ የሚፈልጉትን መርጠው የለ?”
“እሱማ ልባቸው የፈቀደውን መርጠዋል። ግና ይሄ ንቢቱን የመረጠው አንድ ሰው ማነው ከቀዬው ትዕዛዝ እና ስምምነት እንዴት ሊወጣ ቻለ ብሎ ነው ሰዉ ጭንቅ የገባው።” አለኝ።
አንድ ነጥብ ሁለት
በዚሁ ቀበሌ የመረጡትን መርጠው ካበቁ በኋላ ኢህአዴግ “ተጭበርበሪያለሁ” ብሎ ምርጫው ካልተደገመ ሞቼ እገኛለሁ አለ። (አሉ… ይቺ እንኳ “አሉ” ናት) ታድያ ሰዉ በሙሉ በምን ተስማማ መሰላችሁ… “እኛ ዳግሞሽ ምርጫ አንገባም። ከፈለጋችሁ ገበያ ለይ እንሰብሰብና ንቢቷን የሚል ካለ አለሁ ብሎ ይቆጠር እንጂ አንድግዜ የመረጥነውን መርጠናል።” አሉ (አሉ።)
ሁለት
አዴት አካባቢ በሆነው ቀበሌ ደግሞ ምርጫው ተጠናቆ ማታ ላይ ድንገት መብራት እልም ብሎ ጠፋ። ይሄኔ “ካርድ ሳይቆጠር አንሄድም” ብሎ የነበረው የአካባቢው ህዝብ ባትሪ ፍለጋ መተራመስ ያዘ። ባትሪው ተገኘ። ሲበራ ከታዛቢዎች መካከል አንዱ የኢህአዴግ ቀንደኛ ተከራካሪ የነበረው ሰውዬ ጠፍቷል። የት ገባ? ቢጠሩት ቢፈለጉት የት ይገኝ!? መብራቱ ከመጥፋቱ በፊት አጠገባቸው ነበረ። ታድያ የት ገባ?
ትንሽ ቆይቶ መብራት መጣ ይሄን ግዜ አንድ ሰውዬ በአካባቢው ሰዎች ማጅራቱ ተጨምድዶ አንዳች ነገር ታቅፎ፤ “ይሄ ሌባ” እየተባለ ወደ ምርጫ ጣቢያው ገባ። ሰውየው “የት ጠፋ?” ብለው ሲጨነቁለት የነበረው አፍቃሪ ኢህአዴግ ነበር። ምን አድርጎ ነው? ተብሎ ሲጠየቅ ለካስ መብራት እንደ ጠፋች ኮሮጆ ይዞ ነበር የተሰወረው። ድንገት የአካባቢው ሰዎች እጅ ከፍንጅ ይዘው ማጅራቱን ጨምድደው አመጡት እንጂ!
ሶስት
ምርጫው አለቀ እና እነዛ ቀውጢ ቀናት መጡ። ፖሊሶች ማንኛውንም ጎረምሳ እየወሰዱ በየእስር ቤቱ ይከቱት ጀመር። በአንዱ የክፍለሀገር ከተማ የሚከተለው ሆነ፤
ወጣት ልጃቸው የታሰረባቸው አባት ወደ ፖሊሶቹ አዛዥ ሄደው “እባክህ የኔ ጌታ የኔ ልጅ ምንም የሚያውቀው ነገር የለም ለራሱ ህመምተኛ ነው ልቀቁልኝ” ብለው ይጠይቃሉ። ፖሊሱም ትኩር ብሎ እያያቸው “የእርስዎ ልጅ ምንም ውስጥ እንደሌለበት ለማወቅ ትንሽ ግዜ ያስፈልገናል። አሁን ገና እየተረጋገጠ ነው” ብሎ ይመልስላቸዋል። አባትም በአዕምሯቸው “እየተረጋገጠ ነው…” የምትለው ቃል አቃጨለችባቸው። ከዛ ደግመው ጠየቁት፤ “ካልተረጋገጠ አይለቀቀም…?” “አዎ መጀመሪያ መረጋገጥ አለበት” አላቸው ፖሊስ ኮስተር ብሎ “አይ አበሳዬ በሉ እንግዲያስ አደራ እጁ በሽተኛ ነው ስትረጋግጡት ተጠንቀቁልኝ… በስንት ወጌሻ ነው የተሻለው” በማለት የነሱ ማረጋገጥ መረጋገጥ መሆኑን ነግረዋቸው እያዘገሙ ሄዱ።
አራት
በዘጠና ሰባቱ ምርጫ ጦስ ስለመጡ አስቂኝ ነገሮች ወዳጃችን በኋይሉ ገብረ እግዚአብሄር “ኑሮ እና ፖለቲካ” በተባለው መፅሀፉ ውስጥ ካጫወተን ደግሞ ትንሽ እንቀላውጥ፤
በግርግሩ ሳብያ ፖሊሶች ማታ ማታ በእያንዳንዱ ሰው ቤት እየገቡ ድምፁ ጎርነን ያለ ጎረምሳ ሁሉ እያፈሱ ይወስዱ ነበር። ታድያ በአንዱ ማታ በአንዱ ቤት ፖሊሶቹ ሲገቡ፤ ጀርመን አገር ያሉት የልጆቹ አባት በቴሌቪዥን የሚያዩት ነገር ረብሿቸው ስልክ ሲደውሉ እኩል ሆነ። ይሄን ግዜ በፖሊሶቹ ዘው ብሎ መግባት የተደናገጡት ልጆች ስልኩ ሲያምባርቅ በፍርሃት ያዩት ጀመር። ይሄኔ አንዱ ቆፍጣና ፖሊስ አንዱን የቤቱን ጎረምሳ “ስልኩን አንሳ” ብሎ አዘዘውና የሚያወራውን ለመስማት ጠጋ ብሎ።
“ሃሎ”
“ሃሎ”
“የምን ጦርነት ነው የምሰማው ልጆቼ ተረፋችሁ?”
ልጅ የሚመልሰው ጠፋበት ትንሽ እንደማሰብ አለና፤ “አባዬ ምንም ችግር የለም። ሁላችንም ደህና ነን። ፖሊሶች እቤታችን ድረስ መጥተው እየተንከባከቡን ስለሆነ አታስብ!” በማለት መለሰ አፉ በፍርሃት እየተሳሰረ።
አምስት
በአመቱ ሰሜን ወሎ ፍላቂት ላይ ትንሽ ቆይታ አድርጌ ወደ ጎንደር አርማጭሆ ዘልቄ ነበር።
አምስት ነጥብ አንድ
ፍላቂት
የፍላቂት ህዝብም እንደመላው የሀገሪቱ ህዝብ ሁሉ የመረጠው ቅንጅትን ነበር። ታድያ በዛው አመት የአካባቢው ገበሬ ሁለት አይነት ወከባ ነበረበት። አንዱ ማዳበሪያ እና የመሳሰሉትን አገልግሎቶች ሲጠይቅ የየቀበሌው ካድሬዎች “ቅንጅት ይስጣችሁ” እያሉ የሚያጉሏሏቸው ሲሆን ሌላው ደግሞ “ምን አድርገን ነው እኛን ያልመረጣችሁን?” የሚል ስብሰባ ነበር። ታድያ ለምን አልመረጣችሁንም? በሚለው ላይ የሰማናት ቀልድ በጣም ታዋቂ ሆናለች። እዚህ ላይ እርሷን ሳያነሱ ማለፍ አግባብ አይደለም።
ካድሬው፤ “እኛ እስከዛሬ ትምህርት ቤት ሰርተንላችሁ… ጤና ጣቢያ ገንብተንላችሁ… መንገድ ጠርገንላችሁ… ለምንድነው ያልመረጣችሁን?”
ገበሬዎቹ፤ “እግዜር ይስጣችሁ ደህና አድርጋችሁ ሰርታችሁልናል! አሁን ግን ይበቃችኋል እናንተም ይደክማችኋል አረፍ በሉ እኛም ትንሽ አረፍ እንበል!”
አምስት ነጥብ ሁለት
ጎንደር
ጎንደር አርማጭሆ ስንደርስ ስለ አርበኛ ግንባር ዝና ሰማን። የአካባቢው ሰው የመንግስት ታጣቂው ሳይቀር አርበኞችን የሚያነሳቸው በመልካም ነው። ተኳሽነታቸውን እና ስነምግባራቸውን አውርተው አይጠግቡም። አንዱ የመንግስት ታጣቂ ስለ ግንቦት ሰባቱ ምርጫ እንዲህ አወጋኝ፤
“እኛ ገና ከጀምሩ ምርጫ ምርጫ መባሉ ደስ አላለንም ነበር። በስብሰባ ላይ ከወረዳ ለመጡትም ነገረናል። ‘ሰዉ ያሻውን ይምረጥ ካላችሁ አይሆንም፤ ኋላ መዋረድ ይመጣል። ሰዉ ሆድ ስለባሰው አንድ እንኳ የሚመርጣችሁ አይገኝም። ስለዚህ ዝም ብለን እንደቀደመው ግዜ እዚች ላይ አጥቁሩ እያልን እኛው እንምራቸው እና ንቢቱን እናስመርጥ።’ ብለን ብንላቸው “የለም ዲሞክራሲ ነው።” አሉን ከዛስ ምን ሆነ አትለኝም…? ሁሉም ሆ ብሎ ቅንጅቱን መረጠ። ከዛልህ “እኛን በአግባቡ ስላልቀሰቀሳችሁ ነው” ብለው ብዙ ጓዶቻችንን እስር ዶሏቸው። ኋላ ያልታሰርነው ሆ ብለን ወጣናታ… እንግዲህ ለአርበኛ መግባታችን ነው። “በዛሬው እለት የታሰሩ ጓዶቻችን ካልተለቀቁ ነገ ከጫካ ነን።” ብንላቸው ማምሻውን በኦራል መኪና አምጥተው አስረከቡን!

እኔ የምለው ቀጣዩ ምርጫ መቼ ነው…?

Obama should raise press freedom in Africa food talks (CPJ)

May 16, 2012
His Excellency Barack Obama
President of the United States of America
White House
Via facsimile: +1 202-456-2461
Dear President Obama:
As you prepare to host the G-8 summit and discuss the security of food supplies with leaders from Africa, we call on you to strongly consider the role of an independent press in identifying and assessing agricultural challenges and famine, and facilitating the national and international response to food crises.
Mr. President, as a central example, we urge you to consider the situation in Ethiopia. Under the leadership of Prime Minister Meles Zenawi, Ethiopia has made strides in economic growth and poverty reduction. However, Ethiopia remains one of the foremost recipients of U.S. humanitarian assistance as the country is mired in cycles of drought that leave millions of people vulnerable to hunger. The government routinely downplays the extent of the crisis by denying journalists access to sensitive areas and censoring independent news coverage. This undermines the ability of donor nations and aid groups to raise funds and make decisions about how best to mitigate the disaster. USAID has in the past called on the government of Ethiopia to improve access to those affected for assessing their needs and effectively distributing aid.
An independent press and civil society with the freedom to operate without fear or restriction are particularly necessary in Ethiopia to contextualize official claims about drought and food shortages, improve transparency in aid distribution, and alleviate hunger. During the 1980s, investigative journalists circumvented restrictions and censorship imposed by the then-government of Mengistu Haile Mariam in order to document a deepening famine that official statements denied altogether. As a result, millions of lives were saved.
Furthermore, the free flow of information and open debate could help Prime Minister Meles build national consensus and ensure that the government's policies are the result of broad consultation with all segments of society. We believe such engagement would improve the impact of the government's new strategies to reform Ethiopia's agricultural practices.
Mr. President, we are deeply concerned that Ethiopia's ongoing repression of investigative journalism fuels tensions that threaten the country's relative stability and risk unraveling the economic and social progress registered in recent years. Since 2011, under the guise of a counterterrorism sweep, the government of Ethiopia has brought terrorism and anti-state charges against 11 independent journalists, including blogger Eskinder Nega, who may face life in prison for his writing about the struggle for democracy. Such policies deter reporting on all sensitive topics, including food security.
We request that in launching the G-8 food security agenda, you publicly acknowledge that poverty alleviation and inclusive growth require a free press and encourage Prime Minister Meles to end his repressive practices. Good governance, accountability, and adequate response to crises depend, after all, on listening to citizen voices and independent accounts.As you and your G-8 colleagues take vital steps towards advancing food security, we count on you to ensure that the free flow of information is a priority.

Sincerely,

Joel Simon
Executive Director

CC:
H.E. François Hollande, President of France
H.E. Vladimir Putin, President of Russia
H.E. David Cameron, Prime Minister of the United Kingdom
H.E. Stephen Harper, Prime Minister of Canada
H.E. Mario Monti, Prime Minister of Italy
H.E. Yoshihiko Noda, Prime Minister of Japan
H.E. Angela Merkel, Chancellor of the Federal Republic of Germany
H.E. Yayi Boni, President of the Republic of Benin and Chairperson of the African Union
H.E. John Atta-Mills, President of the Republic of Ghana
H.E. Jakaya Kiketwe, President of the Republic of Tanzania
H.E. Meles Zenawi, Prime Minister of Ethiopia
Hillary Clinton, Secretary of State of the United States of America
Michael Forman, Deputy Asst to the President and Deputy National Security Adviser for International Economic Affairs
Ertharin Cousin, Executive Director, U.N. World Food Programme
Dr. Kanayo F. Nwanze, President, International Fund for Agricultural Development
Ms. Josette Sheeran, Vice Chairman, World Economic Forum
Rajiv Shah, Administrator, U.S. Agency for International Development
Bono, Co-Founder of ONE and (RED)