Monday, October 29, 2012

ባለፉት 30 አመታት ከኢትዮጵያ ተዘርፎ ወደ ውጭ አገራት ባንኮች የተሻገረው ገንዘብ 450 ቢሊዮን ብር ደረሰ


ጥቅምት ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-አሜሪካ የሚገኘው የማሳቹሴትስ ዩኒቨርስቲ በያዝነው ወር ባወጣው አዲስ ጥናት ከኢትዮጵያ እየተዘረፈ ወደ ውጭ አገራት ባንኮች የተሻገረው ገንዘብ ባለፉት 30 አመታት ውስጥ 25 ቢሊዮን ዶላር ወይም 450 ቢሊዮን ብር መድረሱን ይፋ አድርጓል። ይህ አሀዝ  አገሪቱ ካላት አጠቃላይ ገቢ ውስጥ 84 በመቶ የሚሆነውን የሚሸፍን ነው።
ኢትዮጵያ ከሌሎች የአፍሪካ አገሮች ጋር ሲተያይ የ8ኛ ደረጃነት ብትይም ነዳጅ ከማያመርቱ አፍሪካ አገሮች ጋር ስትወዳደር ደግሞ ቀዳሚ ሆናለች።
አብዛኛው ገንዘብ የሚዘረፈው ወደ ውጭ አገራት ከሚላኩና ከውጭ አገራት ከሚገቡ እቃዎች እንዲሁም በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ከሚልኩት ገንዘብ ነው፡፡
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ስፖንሰርነት ጥናቱን ያካሄደው ፋይናንሻል ኢንተግሪቲ ባለፉት 7 አመታት ከኢትዮጵያ ከ 11 ቢሊዮን ዶላር  ወይም ከ200 ቢሊዮን ብር በላይ መዘረፉን ይፋ ባደረገ አመት ባልሞላው ጊዜ ውስጥ ነው ማሳቹሴትስ ዩኒቨርስቲ አዲሱን አስደንጋጭ ሪፖርት ይፋ ያደረገው።
ከቻይናና ህንድ የተገኘውን ብድር ጨምሮ ኢትዮጵያ ከ200 ቢሊዮን ብር በላይ የውጭ እዳ እንዳለባት መዘገባችን ይታወሳል።
ከኢትዮጵያ በሙስና እና በተለያዩ የንግድ ወንጀሎች  ወደ ውጭ አገር  የሚወጣው ገንዘብ በአገር ውስጥ ባንኮች ቢጠራቀም ኖሮ 3 የአባይን ግድቦችን፣  በመቶዎች የሚቆጠሩ ዩኒቨርስቲዎችን፣ ሆስፒታሎችንና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን መስራት ይቻል ነበር።
በአጠቃላይ ከሰሀራ በታች ካሉ አገራት ከ800 ቢሊዮን ዶላር በላይ ተዘርፎ  በውጭ አገራት ባንኮች መቀመጡ ተመልከቷል።
በአቶ መለስ የቀድሞው አስተዳዳር በኢትዮጵያ ታሪክ ተስምቶ የማይታወቅ ከፍተኛ ገንዘብ ተዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች ተቀምጧል።

የኦሮሞ ፖለቲካ ጉዳይ (ከትናንት እስከ ዛሬ)


አቶ  ቡልቻ ደመቅሣ
የኦሮሞ የፖለቲካ ጉዳይ በየዘመኑ አንድ እርምጃ ወደፊት ሁለት እርምጃ ወደኋላ ሲመሏ ለዘመናት ቆይቷል፡፡ ይህ የሆነው ከአፄ ሚኒሊክ ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ ከዚያ በፊት፣ የኢትዮጵያ ነገስታት ኦሮሞን ለማሸነፍ ስላልቻሉ በየጊዜው እየተጋጩ እንደምንም አብረው ይኖሩ ነበር፡፡ ፋዘር አልሜዳ የሚባለው የፖርቱጋል ቄስ በዚህ ጉዳይ በሰፊው ጽፏል፡፡ ነገር ግን አብሮነታቸው እንደ ገዥና ተገዥ አልነበረም፡፡ ከአጼ ልብነድንግል ጀምረው እስከ ንጉስ ሳህለ ስላሤ የነበሩት አፄዎች ሁሉ ኦሮሞን ለማሸነፍ እና ለመግዛት ያላደሩጉት ጥረት አልነበረም፡፡ የኦሮሞ ፖለቲካ ጉዳይ (ከትናንት እስከ ዛሬ)
ኦሮሞንና ሀገሩን አሸንፈው ለማስገበር የቻሉት አፄ ሚኒሊክ ብቻ ነበሩ፡፡ እሳቸውም ኦሮሞን ለማሸነፍ የቻሉት ከኦሮሞዎች ቀደም ብለው ከፈረንጆች የጦር መሳሪያ ስላገኙ ነበር፡፡ መሣሪያ ያገኙበትም ምክንያት ከእሳቸው ቀድሞ የነበሩት አንዳንድ አፄዎች ለአውሮፓ መንግስታት “ኢትዮጵያ ብቻዋን ክርስቲያን ሆና በአፍሪካ ውስጥ የምትኖር ሀገር ነች” ብለው የአውሮፓውያን መንግሥታትን ስለለመኑና ስላስረዱ የጦር መሣሪያ ማግኘት ቻሉ፡፡ በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አፄ ሚኒሊክ ሸዋን በሙሉ ለመቆጣጠር ሲነቃነቁ ደብረብርሃን አጠገብ በምትገኘው አብደላ በምትባል መንደር ውስጥ ከጎበና ዳጬ ጋር ተገናኙ፡፡ ጎበና ዳጬም በዚያን ጊዜ በኦሮሞ ገዳ ሥርዓት የሉባና የነበዙ አባ ደክር ወዳጅ የነበሩ፡፡ ከአፄ ሚኒሊክ ለጎበና ዳጬ አንድ ነገር ተናገሩ፡፡ “ወደታች ወደደቡብ እንሂድ፡፡ ወደአቢቹ፣ ገላን፣ ጉለሌ፣ አርሲ አብረን እንዝመት፡፡ አንተ የጋላ ንጉስ ትሆናለህ፣ እኔ የኢትዮጵያ ንጉስ እሆናለሁ ተከተለኝ” አሏቸው፡፡ እንደተባባሉትም ወደታች ወደደቡብ መጥተው የኦሮሞን ጎሣዎች መውጋት ጀምሩ፡፡ ጎበናም ራስ ተባሉ፡፡ ነገር ግን አፄ ሚኒሊክ ለጎበና የገቡትን ቃል ሳይጠብቁ ቀሩ፡፡ ጎበናም ብዙ ጊዜ ከተዋጉ በኋላ እየተዳከሙ ሄዱ፡፡ ነገር ግን የሸዋን፣ የወለጋን (በሰላም የገቡ) እና የከፋን (ከፋም በሰላም ገባ) ኦሮሞዎች ካሸነፉ በኋላ አፄ ሚኒሊክ እራሳቸው ጦርነቱን መምራት ጀመሩ፡፡ ራስ ጎበና በቀየሱት መንገድ ሄደው ሌሎች ያልተያዙትን ሀገሮች ያዙ፡፡ ለምሳሌ ሀረርን፣ ውጋዴንን፣ ሱማሌን፣ ቦረናን ያቀኑት ከዚያ በኋላ ነው፡፡ (እኔ አቀኑ እላለሁ አንዳንድ ሰዎች ግን “ኮሎናይዝ” አደረጉ ነው የሚሉት፡፡ እውነቱን ለታሪክ ተንታኞች እንተዋለን፡፡) ይህ ታሪክ አፈታሪክ ነው፡፡ የታሪክ ምሁራን እንደሚሉት አፈታሪክ የተፃፈ ታሪክ ያህል ዋጋ አለው፡፡ አሁን ልክ አይደለም ብሎ መከራከር ዋጋ ቢስ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም ኦሮሞዎች ሁሉ ይህን ያምናሉ፡፡ ያም ሆነ ይህ የታሪኩን እርግጠኛነት የሚያረጋግጠው የራስ ጎበና ሕመም ነው፡፡ (በብስጭት እንደሆነ በእርግጠኝነት የሚናገሩ የእሳቸው ተወላጆች አሉ፡፡)
እኔ እንደብዙ ወገኖቼ ጎበናን አላብጠለጥልም ሰው ስራ መስራት አለበት፡፡ ቤተሰቡን የሚደግፈው የሰራ እንደሆነ ነው፡፡ አለስራ መኖር አይቻልም፡፡ ስለዚህ ራስ ጎበና ስራ አግኝተው ቢሰሩም የፈለጉት ሳይሆን ቀርቶ ታመው ሞቱ፡፡ ይሄ ማንኛቸውም መሪ የሚያረገው ነገር ነው፡፡ አንዳንዱ አላደርግም ብሎ ይሞታል፡፡ ግን ብዙ ሰው ሞትን አይመርጥም፡፡ አፄ ሚኒሊክ ጎበናንም ባያገኙ ማሸነፋቸው አይቀሬ ነበር፡፡ ምክንያቱም በዚህ ጊዜ ከአውሮፓውያን ብዙ የጦር መሣሪያ አግኝተዋል፡፡
ራስ ጎበና ከሚኒሊክ ጋር ያደረጉት ስምምነት ለጊዜው ለኦሮሞ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚሄድ መስሎ ነበር፡፡ ከዚያም በኋላ አፄ ሚኒሊክ ኦሮሞን የገዙበት የባሪያ አገዛዝ ሁለት እርምጃ ወደኋላ እንዲሄዱ አደረጋቸው፡፡ ኦሮሞ ደርግ ላይ ምንም ተስፋ ስላልነበረው የጀነራል ተፈሪ ባንቴ ፕሬዝዳንት መሆን ምንም አልመሰለውም፡፡ ዶክተር ነጋሶ ፕሬዝዳንት ሲሆኑ ለኦሮሞ የተሻለ መስሎ አልታየውም፡፡ ዶክተር ነጋሶም እራሳቸው በስርዓቱ ባለማመን ረግጠው ወጡ፡፡
ከዚያ በኋላ የአፄ ሚኒሊክን የጦር ኃይል መመከት ያልቻለው ኦሮሞ፣ ገባርነትን ለመቀበል ተገደደ፡፡ ሆኖም ግን አፄ ሚኒሊክ ከዚያ በፊት ኦሮሞ ይዞት የነበረውን መሬት ማስለቀቅ ስላልቻሉ ኦሮሞ በአፄ ልብነድንግል ጊዜ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ይዞት የነበረውን መሬት እንደያዘ ቀረ፡፡ እዚህ ላይ እናስታውስ፡፡ የወሎ አሮሞና ትግራይ ውስጥ ያሉት ራያና አዘቦ ኦሮምኛ ቋንቋቸውን እየረሱ አማርኛ ወይም ትግሪኛ መናገር ጀምረዋል፡፡ በአማራ ክልል ውስጥ ያለው ኦሮሞ ዞን ከተፈጠረለት ለምን የራያና አዘቦ ዞን በትግራይ ውስጥ አልተፈጠረም፡፡ ይኼ የሚያሳየው ሕገ መንግስቱ በተፃፈበት ጊዜ (በ1986 ዓ.ም) ህወሓት የነበረውን ፍጹም የበላይነት ነው፡፡
ዛሬ የኦሮሞ ሕዝብ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ቢያንስ 35 በመቶ መሆኑን ሁላችንም እናውቃለን፡፡ ሕዝቡም ወደ ሰላሳ ስድስት ሚሊዮን ይገመታል፡፡ የኦሮሞ መሬት ስፋቱ 387,000 ኪሎ ሜትር ይሆናል፡፡ ማለትም ጀርመንን ያክላል ማለት ነው፡፡
ኢህአዴግ በ1983 ዓ.ም. አዲስ አበባ በገባ ጊዜ ኦነግ አብሮት ስለነበረ ኦሮሞ አንድ እርምጃ ወደፊት እንደሄደ ሊገመት ይችላል፡፡ ምክንያቱም ኦነግ አስራ ስድስት አመት ከታገለ በኋላ ከህወሓት/ኢህአዴግ ጋር አብሮ ሲመለስ አንድ የፀና ስምምነት ተፈራርሞ የመጣ መስሎ ለኦሮሞዎች ታየ፡፡ ስለዚህ ኦሮሞዎች ለጊዜውም ቢሆን ተረጋጉ፡፡ ነገር ግን ሳይቆይ ኦነግ ወደ ትግል ተመለሰ፡፡ በአገር ውስጥ ያሉ ኦሮሞዎች ኦነግ ፌደራሊዝምን የተቀበለ – መስሎአቸው ስለነበር ካገር በመውጣቱ አዘኑ፡፡ ከዚህ ይልቅ በሀገር ውስጥ ሆኖ ስለሰብዓዊ መብት፣ ስለእኩልነትና፣ ስለዲሞክራሲ መታገል ነበረበት ብዬ አስባለሁ፡፡
ኦነግ ተመልሶ ከአገር ሲወጣ “ኢህአዴግ ውስጥ ገብቼ አባል አልሆንም” የሚለውን ኦሮሞ ሁሉ ‹‹የኦነግ አባል ነህ›› እያሉ በጅምላ ማሰር፣ አንዳንዱን መግደል፣ የእለት ተዕለት ትእይንት ሆነ፡፡ በዚች አጭር ጽሑፍ ውስጥ የሞቱትን፣ የታሰሩትን መቁጠር አይቻልም፡፡ ነገር ግን እኔ የኦፌዴን መሪ በነበርኩበት ጊዜ ከትልልቆቹ ስራዎቼ መካከል ዋናው ስለኦሮሞ መሞት፣ መታሰር እና መሰቃየት ለኦሮሚያና ለፌዴራል መንግስታቱ እድፍ ነበር፡፡ እንዲያውም አንድ ጊዜ ለማስመሰል የፌዴራል መንግስቱ፣ ኦፌዴንና ኦህዴድ የጋራ ኮሚቴ አቋቁመው ስለነኚህ ችግሮች ያጥኑና የጥናታቸውን ውጤት ያቅርቡ ተብሎ አንድ ኮሚቴ ተቋቁሞ ነበር፡፡ መጀመሪያውኑ ከልብ ስላልሆነ ኮሚቴው ቶሎ ፈረሰ፡፡
ኦሮሞ የገዳን ሥርዓት ለመተው የተገደደው በመንግስት እና በዘመኑ የኢኮኖሚ ሥርዓት ለውጦች ምክንያት ነው፡፡ የገዳ ሥርዓት እንዳለ ሥራ ላይ መዋል በአሁኑ ዘመን አይቻልም፡፡ ምክንያቱም በአሁኑ ዘመን ወጣቶች ሁሉ በተወለዱበት ሥፍራ አይቆዩም፡፡ ለስራና ለትምህርት ከተወለዱበት ወጥተው ወደሌላ ስፍራ ይሄዳሉ፡፡ አንዱ ትውልድ ሌላውን ትውልድ በሙሉ ካልተካ የገዳ ሥርዓት አይሰራም፡፡
ብዙ የኦሮሞ ምሁራን የገዳን ሥርዓት የሚወዱበት ምክንያት ሥልጣን ላይ ያለው ትውልድ አዲሱ ትውልድ ለስራ ሲዘጋጅ ቦታውን ለቆ መሄዱ ለዲሞክራሲ ጥሩ አስተዋጽኦ ያደርጋል በማለት ነው፡፡ ለሁሉም በአሁኑ ጊዜ ማንም በተወለደበት ቦታ ለብዙ ጊዜ ቀጥሎ ስለማይኖር የገዳ ሥርዓት ሃሳቡ ሲፀነስ በሰራበት መልኩ አሁን ሊሰራ አይችልም፡፡
የኦሮሞ ጥንታዊ ሀይማኖት ዋቄፈታ ሲሆን፤ ይኼም ብዙ ሰዎች እንደሚሉት ወይም እንደሚመስላቸው ለፍጥረት መስገድ አይደለም፡፡ ወንዝ አጠገብ፣ ታላቅ ተራራ አጠገብ፣ ታላቅ ዛፍ ስር ዋቄፈታ ማድረግ እንደዚህ አይነት ታላቅ ፍጥረትን ለፈጠረው አምላክ መስገድ ነው፡፡ አማኞቹ እንደሚሉትም እግዚአብሔር ራሱን የሚገልፀው በታላላቅ ፍጥረቶች በኩል ነው፡፡ እዚህ ላይ ስለዋቄፈታ ያነሳሁት ባለፈው አስር ቀን ውስጥ ኦሮሞዎች ቢሾፍቱ ሀይቅ አጠገብ የተለመደውን ኢሬቻ ለማድረግ የተሰበሰበውን ህዝብ (ሶስት ሚሊየን ህዝብ ነበር ተብሏል) ፖሊስ በሀይል በህዝቡ መሃከል ለብሶ የለበሳችሁት ልብስ የኦነግ ባንዲራ ነው በማለት በመደብደብ፣ በመርገጥ እና ልብሳቸውን በማስወለቅ ጭምር ከባድ ጉዳት አደረሰባቸው፡፡ ይሄ አድራጎት በኦሮሞዎች ዘንድ እንደ ታላቅ ሀጢያት እና እግዚአብሔርን እንደ መዳፈር መስሎ ታየ፡፡ ይህ ሥርዓት በጠባዩ ለእነርሱ ሀይማኖታዊ ነው፡፡
የህዝብን ድምፅ የሚሻ፣ ሰላምን የሚፈልግ እና ትብብርን ከህዝብ የሚጠብቅ መንግስት እንዲህ አይነት ፀረ-ባህልና ፀረ-ህዝብ ወንጀል አይፈፅምም፡፡ ለጊዜው ለዚህ አድራጎት የምናየው ምላሽ ላይኖር ይችላል፡፡ ነገር ግን ኦሮሞ ይሄንን አድራጎት ይረሳል ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው፡፡ ማንም ህዝብ ይህ ቢደርስበት ዝም የሚል አይመስለኝም፡፡ የፌደራሊዝም ፅንሰ-ሀሳብ የተዋወቀው ይህን መሰሉን በደል ለማስቀረት ነበር፡፡
ይህ ሁኔታ በፌዴራሊዝም ስርዓት የሚያምኑትን የኦሮሞ ምሁራን አቋም የሚፈታተን ነው፡፡ ምክንያቱም ኦሮሞ ከሌላው ህዝብ ሁሉ ተለይቶ እንደባእድና ጠላት እየታየ መኖር ቢመረውም ከቀሪዎቹ የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር ተስማምቶ በፍቅር መኖር ይፈልጋል፡፡
የኦሮሞ ጥንታዊ ሃይማኖት ዋቄፈታ ነበር፡፡ አሁንም በዋቄፈታ የሚያምኑ ኦሮሞዎች ቁጥራቸው በጣም ብዙ ነው፡፡ ዋቄፈታ ከክርስትናም ሆነ ከእስልምና የተለየ የኦሮሞ የጥንት እምነት ነው፡፡ እነዚህ ሁሉ ልዩነቶች ቢኖሩም ብዙዎቻችን የኢትዮጵያ አካል ሆነን በፌዴራሊዝም ሥርዓት እንኖራለን ብለን በቆራጥነት ተነስተናል፡፡ እንዲህ የሚለው ወገን ግን ዛሬ ድምፁ እየተዳከመ ሄዷል፡፡ ህዝብ መናቅ እንደ ቀላል ነገር ሆኖ እየታየ ነው፡፡ ቢሾፍቱ ላይ ለኢሬቻ የመጡትን አማኞች የኦነግን ባንዲራ ለብሳችኋል በማለት ደብድበው ልብሳቸውን የነጠቋቸው ሰዎች ራቁታቸውን ከስፍራው ሲወጡ ታይተዋል፡፡
የኢሬቻን በዓል መንግስት ለምን እንደፈራው አይታወቅም፡፡ ከዚህ በፊት ለዘመናት በየዓመቱ ሲደረግ ቆይቷል፡፡ አሁን የመንግስት የፀጥታ ሰራተኞች አንድ ቡድን ያደመው ወይም ያዘጋጀው ተንኮል ኖሮ የደረሱበት ነገር ኖሮ ይሆን? አናውቅም፡፡ ጨርሶ ኢሬቻን ለማጉላት አይመስለኝም፡፡
ሌላ የኦሮሞ ቅሬታ አለ፡፡ ከአቶ መለስ ሞት በኋላ የመንግስት ብወዛ ተደርጎ ነበር፡፡ ለጊዜውም ቢሆን የመንግስትን አቅጣጫና ፕላን የሚያመላክቱ ብወዛዎች ተፈፅመዋል፡፡ እዚህ ውስጥ ኦሮሞዎች ምንም ሚና አለመጫወታቸው ብዙ ሰዎችን አስገርሟል፡፡ ከሃገሪቷ አጠቃላይ ህዝብ 35 በመቶ ከመሆናቸው ባለፈ ምድራቸው እጅግ በጣም ሰፊና ሀብታም ሆኖ ሳለ፤ ዛሬ ለኦሮሞ ህዝብ ዝቅ ያለ ግምት እየተሰጠው ነው፡፡ ይህ ሁሉ የሚሆነው ለምንድን ነው? የጥያቄው መልስ ያለው ኦሮሞ ህዝብ ዘንድ ነው፡፡ ኦሮሞ ሙሉ የዴሞክራሲ መብቱን የሚጠይቅበት ጊዜ ቅርብ ነው፡፡ ኦሮሞንና የደቡብ ህዝቦችን ማጥቃትና መናቅ በምንም ዓይነት መንገድ ፍትሀዊ አይሆንም፡፡ የሚመጣው የኦሮሞ ትውልድ እንደዛሬው ትውልድ ዓይናፋርና ዝምተኛ አይሆንም፡፡
ፓርላማ ውስጥ እኔና ጓደኞቼ ለምንድን ነው ኦሮሞ የሚጠመደው? ለምንድን ነው ኦሮሞ እንደ ጠላትት የሚታየው? ብለን ስንጠይቅ መልስ አላገኘንም፡፡ ነገር ግን በሽብርተኝነት ህጉ መሠረት ኦነግን ትደግፋላችሁ በማለት በፍፁም ከኦነግ ጋር ግንኙነት የሌላቸውን ሰዎች በብዛት ታስረው ዛሬ እስር ቤት ውስጥ ይማቅቃሉ፡፡ ፍርድ ቤት የእነኚህን ሰዎች ጥፋት በጥልቀት ቢመረምር አንድም የሚያስከስስ ስራ አልሰሩም፡፡ አንዳንዶቹ የፖለቲካ ነፃነት ያለ መስሏቸው ህዝብን ለማደራጀት እንዲሁም የፖለቲካና የኢኮኖሚ ትምህርት ለመስጠት ሲሞክሩ ያለአንዳች ጥያቄ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተወስደው ብዙ ቀናት ከማቀቁ በኋላ ፍርድ ቤት ይቀርቡና ለረጅም ጊዜ እስር ቤት እንዲቆዩ ይደረጋል፡፡ በቀለ ገርባ የሚባል የኦፌዴን ም/ፕሬዝዳንት እነሆ ያለአንዳች ጥፋት ዛሬ ቃሊቲ እስር ቤት ውስጥ ይማቅቃል፡፡ የተያዘው ስለ ሰብዓዊ መብት ኢትዮጵያን ሲጎበኙ የነበሩ ፈረንጆች ስለአነጋገሩት ነው፡፡ በሕገ መንግሥቱ የተፃፈው ታምኖበት ነው ወይንስ አንዳንድ ገር ሰዎችን ለማታለል ነው፡፡ ዜጋ የሚያዝበት ሁኔታ፣ ተይዞ ፖሊስ ጣቢያ የሚቆይበት ጊዜ፣ ፍርድ ቤት የሚቀርብበት ጊዜ፣ ፍርድ ቤትም ጉዳዩን በቀጠሮ የሚያቆይበት ጊዜ ሁሉ በሕገ መንግሥትና በሲቪልና ክሪሚናል ፕሮሲጀር ኮድ ተጽፏል፡፡ እነኚህ ሕጎች ሁሉ በየቀኑ እየተጣሉ ነው፤ በትንሹ ሳይሆን በብዛት ነው፡፡ ይህን ሁሉ አቶ መለስ ከዕረፍታቸው በፊት ያውቁ ነበር፡፡ እኔ ራሴ ከእኔ ቢሮ ስለሚሞቱት ሰዎች፣ ስለሚያዙ ሰዎች፣ ስለሚታሰሩ ሰዎች፣ ብዙ ጊዜ ለክልሉ ፕሬዚዳንት እና ለጠቅላይ ሚ/ር ቢሮ ጽፌአለሁ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዛሬም በእሳቸው ቦታ የተተኩ ሰዎች በኦሮሞ ላይ የሚደርሰውን ግፍ ያውቃሉ፡፡ ነገር ግን የሕዝብ መብት እንዳይደፈር አንድ ወገን ለይቶ ማጥቃት ተገቢ አለመሆኑን የወጣ አዲስ ትዕዛዝ አላየንም፡፡ ለወደፊትም ላናይ ነው?
ማስታወሻ
ከዚህ አጭር ጽሁፍ ጋር አያይዤ ለአንባቢያን የማሳስበው ነገር አለ፡፡ አንዳንድ ወዳጆቼ አንድ ጥያቄ ሁልጊዜ ይጠይቁኛል፡፡ “ለምን ሁልጊዜ ስለ ኦሮሞ ብቻ ትጽፋለህ?” መልሶቼ ባያጠግቡም ሁልጊዜ ተመሳሳይ ናቸው፡፡ “እኔ ደህና አድርጌ የማውቀው ስለ ኦሮሞዎች ስለሆነ ነው፡፡ የኢህአዴግ መንግስትም ኦሮሞን ለይቶ ስለሚያጠቃ ነው፡፡ ሌላውንም ህዝብ አጥቅቷል፡፡ ለምሳሌ ሲዳማና ጋምቤላ በጣም ተመቷል፡፡ ስለነሱ በዝርዝር የሚያውቁት መጻፍ ይገባቸዋል፡፡ እኔ ስለ ኦሮሞ ስጽፍ ኦሮሞ የኢትዮጵያ አካል አይደለችም በማለት አይደለም፡፡ ነገር ግን ህግና ሥርዓት ባለበት ሀገር ማንም ቡድን፣ ብሔር ወይም ሌላ ስብስብ መጠቃት የለበትም፡፡ ፌደራሊዝም ስራ ላይ እንዲውል እንደዚህ አይነቱን የተዛባ አመለካከት እና አያያዝ ለመከላከል ነበር፡፡ እኔ ለኦሮሞ የምፅፍበት ሌላ ምክንያት የለኝም፡፡ ግን ሌላም የኢትዮጵያ ጉዳይ ደጋግሜ እጽፋለሁ፡፡

መስማት የተሳነው፡ ስብሃት ነጋ

ከማተቤ መለሰ ተሰማ
በአጼ ምኒልክ ዘመን፡ አንድ ኢትዮጵያዊ፡ በድንገት መስማት ይሳነዋል አሉ፡ ሰውየው እድሜ ጠግቦ እስከሚሞት፡ የምኒልክ፣ የእያሱ፣ የዘውዲቱ ንግስና አልፎ፡ ከሀይለ ስላሴ የግዛትsebehat nega one of the founders of TPLF ዘመን አጋማሽ ድረስ ቆይቶ ነበርና፡ ጆሮው መስማት ከማቆሙ በፊት የነበረው ሁሉ እንዳለ፡ የቀጠለ መስሎት፡ በምኒልክ አምላክ እንዳለ ነው የሞተው ይባላል። በአጠቃላይ ስነምግባሩ፡ ሲታይ ከሰው ተወልዶ ከእንስሳት ጋር እንዳደገ፡ በግልጽ የሚመሰክርበት፡ ስብሃት ነጋም፡ እንዳይሰማ ጆሮው የደነቆረው፣ እንዳያነብ አይኑ የታወረው፡ ደደቢት ከነበረበት ጊዜ ጀምሮ ሳይሆን የሚቀር አይመስለኝም። ምክናያቱም ዛሪ ሕዋሃት የማስመሰያ ካባውን አጥልቆ፡ ኢትዮጵያዊ ለመባል እየጣረ ባለበት ወቅት ስብሃት ከ21 አመት በሗላ የሚናገረው ሁሉ፡ በምኒልክ ሲል እንዳለፈው ሰው ደደቢት በነበረበት ጊዜ ሲሰበክ የነበረውን፡ የኢትዮጵያን ህዝብ ማዋረድንና አማራንና የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖትን  ማጥላላት፣ ስለአከተመለት ስርአት ሰለደርግ ማውራትን ነው። ከዚህ አንጻር ሲታይ፡ በአሁኑ ወቅት ሰውየውን በጥሞና ለሚከታተለው ሰው፡ ዘመናት ጥለውት ከንፈው እሱ አንድ ቦታላይ ቆሞ ለብቻው እየቆዘመ እንዳለ ለመገንዘብ አያዳግተውም።
ለነገሩማ እርጅናም፡ በአንዳንድ ሰዎች ላይ የህሌና ሚዛንን ማዛባቱ ባይቀርም፡ ስብሃትን ግን ከእድሜው በላይ ያደነቆርው፡ ቀን ሲያኝከው የሚውለው ጫት፣ ማታ ተዘፍዝፎበት የሚያድረው አረቄ ነውና፡ እነዚህ ሁለት አድገኛ የሰው ልጅ የአካልም የአእምሮም ጠንቅ የሆኑና አቅልን የሚያስቱ ነገሮች፡ ማየትና መስማቱን ብቻ አይደለም፡ ህይወቱንም አለመንጠቃቸው የሚያስገርም ነው።
ውድ አንባብያን፡ በዚህ ጽሁፊ ስብሃት ነጋን አንተ እያልሁ የምገለጸው፡ የክብርን ዋጋ ለማያውቅና፡ በ90 ሚሊዮን የሚገመተውን ጭዋና አስተዋዩን የኢትዮጵያን ህዝብ በጠቅላላ ለሚዘልፍ ሰድ አክብሮት መስጠት፡ እራስን እንደማዋረድ ስለምቆጥረው መሆኑ ይታወቅልኝ። ለምን የሚል ካለ መልሴ፡ ሌላውን ትቸ 19/10/2012 የጀርመን ሶሻሊስት ፓርቲ ባዘጋጀው፡ የአፍሪካ የውይይት መድረክ ሰብሰባ ላይ ተገኝቶ በነበረበት ወቀት ከተናገረው 2ቱን ለአብነት ብጠቅስ በቂ ይመስለኛል። ስብሃት ነጋ ስለ ኢትዮጵያ ህዝብ መጻሂ እድልና የፓለቲካ ምህዳር እንዲያብራራ ለቀረበለት ጥያቄ፡ በተለመደውና ስነምግባር ባልገራው አንደበቱ የሰጠው ከጥያቄው ጋር ምንም ግንኙነት የሌለው መልስ፡ 1ኛ/ ስነስራት የሌለውን የኢትዮጵያን ህዝብ ስራት ለማስተማርና፡ የደርግ እርዝራዦችን፡ ለመቆጣጠር በዙ ጊዜ አሳልፈናል። 2ኛ/ የኢትዮጵያ ህዝብ ለዲሞክራሴ ብቁ አይደለም የሚል ነበር። ማን ይሆን፣
አውቃለሁ መራር ነው መራብ መጠማት፣
ቁስሉ አይጸናም እንጅ ደግሞ እንደ ውርደት
ያለው? እንዲህ ተዋረደ፡ ደጉ፣ እሩህሩሁ፣ ጭዋው፣ አትንኩኝ ባዩ፡ የኢትዮጵያ ህዝብ፡ ይገርማል፡ አርቆ በማሰቡ፣ በመታገሱ፣ ከወያኔና ጋጠወጥ መሪዎቹ፡ የተመለሰለት ይህ ነው። ለመሆኑ ስብሃት ነጋ ማነውና ነው የኢትዮጵያን ህዝብ ስራት የሚያስተምረው? እሱስ ስራት ለማስተማረ ቀድሞ ነገር ስራት አለው ወይ? ይህን ያህል በእብሪት የተወጠረበትስ ምክናያት ምንድን ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን ማንሳት የግድ ከሚልበት ደረጃ ላይ የደረስን ይመስለኛል። ከኤርትራዊ እናቱና ከአድዋው አባቱ የተወለደው፡ የዛሪው ስብሃት የትናንቱ ወልደ ስላሴ ነጋ፡ ወደትግል ከመግባቱ በፊት የሚያከብረውና የሚያፈቅረው፡ ከአባቱ ይልቅ እናቱን እንደነበርና፡ አሁንም ሆነ በትግሉ ወቅት፡ ከምር የሰራውና እየስራ ያለው ከኢትዮጵያ የልቅ ለኤርትራ እንደነበርና እንደሆነ በብዙ ማስረጃዎች እያስደገፉ ምስክርነታቸውን ሲሰጡ የኖሩ በቅርብ የሚያውቁት ሰዎች እነዳሉ አስታውሳለሁ።
ስብሃት ወይንም ወልደ ስላሴ፡ ለኢትዮጵያውያን የነበረውን ጥላቻ፡ በገቢር ማሳየት የጀመረውም፡ ሜዳ በነበረበት ጊዜ፡ ወደትግሉ የሚቀላቀሉ ሴት እህቶቻችንን አስገድዶ እየደፈረ፡ ሲያረግዙ እንዳያጋልጡት በመግደልም እንደነበር ብዙ ቀራቢው የነበሩ ሰዎች ተናግረውታል፡ ቀጥሎ ወያኔ ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረ በሗላም፡ ከመለስ ዜናዊ በስተጀርባ ሆኖ ለ21 አመታት በኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ላይ ለተፈጸመው መለኪያ መስፈርት፡ መግለጫ ቃላት፡ ለማይገኝለት ግፍ፡ ቀላል ሚና አልነበረም፡፡ ሌባ ሲካፈል እንጅ፣ ሲሰርቅ አይጣላም፡ እንደሚባለው ሁሉ፣በቅርብ፡ ከአዜብ መስፍን ጋር፡ በጥቅም መጋጨት እስከጀመሩ ጊዜ ድረስ፡ መለስ ያለስብሃት ይሁንታ፡ የሰራውና የሚሰራው እንዳልነበር የታወቀ ነው።የዛሪው የኢትዮጵያ ህዝብ ስራት የለውም፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ለዲሞክራሴ ብቁ አይደለም ወ.ዘ.ተ. የሚለው ዘለፋው፡ የመነጨውም፡ከዚያ  ከቆየው የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊያን ጥላቻው ነው።
ያረጀ የልማድ ፈረስ ጋላቢውና፡ በክፋት፣ በቅናትና በምቀኝነት፡ ለተበከለ፣ በመንፈስም የታወረ፣ በአልኮል መጠጥ ብቻም ሳይሆን፡ በእርኩስ ምኞትም የሰከረ፡ አእምሮ ባለቤት የሆነው፣ እንዲሁም ከክዕደት ጋር ጡት የተጣባው፡ ስብሃት ነጋ፡ የበቀል ጥሙን ለማርካት የነደፈው መረሃግብር ተሳክቶለት፡ ኢትዮጵያ በጥፋት፣ ህዝቧ በፍርሀት እንዲዋጡ፣ ምድሯም ሲቃይ ተዘርቶ መከራ የሚበቅልባት፣ ምሪትና ዋይታ የሚታጨድባት፣ ሞት፣ በሽታ፣ እራብና እርዛት፣ በገፍ የሚመረትባት፣ የሰው ልጅ ስብናው፡ እየበሰበሰ፣ ማንነቱ ሰርዶ እየለበሰ ያለባት፡ ምድራዊ ጋነብ እንድተሆን፡ ካደረጓት ሰዎች ግንባር ቀደሙ ለመሆን በቅቷል።
ያንን ሁሉ በደል ሲፈጽም፡ ዝም በመባሉም ነው፡ እንደዚህ ለከት የለሽ፡ አፉን ለመክፈት የበቃው፡ እኛስ መቸይሆን ትግስታችን የሚያበቃው? መቸ ይሆን ውርደቱ የሚያመን? መቸይሆን በሌሎች ኪሳራ አትራፊ ለመሆን የፓለቲካ ሂሳብ መስራታችንን፡ አቁመን የተነጠቅነውን ማንንታችነን፡ ለማስመለስ የህይወት መሷዕትነት መክፈልን፡ ምርጫችን የምናደርገው? መቸይሆን እንደዚህ እየተዋረዱ፡ ቆሞ ሲሞቱ ከመኖር ይልቅ፡ ሞትን በሞት ሽሮ ማለፍ ሃያው እነት ነው፡ የሚለውን ብሂል ስራላይ የምናውለው? ውድ አንባብያን እስኪ ለአፍታ ቆም በማለት ውስጣችነን እንፈትሽ፡ እኔም፣ አንተም ሆንህ፣ አንች፡ ከስብሃት ነጋ የምናንስበት ምን ነገር አለ?????
ጥቅምት ወር 2012