Friday, November 23, 2012

በአዲስ አበባ የሚገኘው የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ሊፈርስ ነው


በአዲስ አበባ የሚገኘው የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ሊፈርስ ነው

ህዳር ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:- በአዲስ አበባ የሚገኘው የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልትሊፈርስ ነው:፡ ዛሬ በሸገር ኤፍ ኤምላይ ቀርበው መግለጫ የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሀላፌ እንዳሉት ከባቡር ስራ ጋር በተያያዘ የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ይነሳል::
ሆኖም መነሳቱ በጊዜዊነት ነው ሀዲዱ ከተሰራ በሆላ ወደቦታው ይመለሳል ብለዋል::
የኢሳት ምንጮች ከፕሮጀክት መሀንዲሶች አካባቢ የተገኘን መረጃ ጠቅሰው እንደገለጡት የሀዲዱ ዲዛይን ላይ ለሚነሳው የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ላይ ቦታ የለም እናም ሀውልቱ እንደፈረሰ የመቅረቱእድል የሰፋ ነው ሲሉ ገልጠዋል:፡ በተያያዘ መረጃ በዲዛይን ላይ የአጼ ሚኒሊክ ሀውልት ተመሳሳይ እጣ ፈንታ ሊገጥመው እንደሚችል ታውቆል:: መንግስት ጊዚያዊ ነው ቢልም ዲዛይኑ የሚያረጋግጠው ግን ሀውልቶቹ እስከወዲያኛውም ወደቦታቸው እንደማይመለሱ ነው::
ከፍተኛ ተቃውሞ የቀረበበትና በሲኖዶስ እንዲፈርስ የተወሰነው የአቡነ ጳውሎስ ሀውልት ቆሞ የታላቁ አርበኛና መስዋእት አቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ሊፈርሱ ነው መባሉ በእርግጥ አነጋጋሪ ሆኖል።
Abune Petros was born in 1892 in a farmer family in the city of Fiche