Saturday, April 6, 2013

ትግል...ሽንፈት፤... ድል፤ ሽንፈት...


ትግል...ሽንፈት፤... ድል፤ ሽንፈት...
(ከተመስገን ደሳለኝ )
ከምሽቱ አንድ ሰአት አልፏል፤ የእጅ ስልኬ ደጋግሞ ቢጮኽም ትኩረት አልሰጠሁትም፡፡ ከጥቂት ሰከንዶች
ፋታ በኋላ የቢሮዬ ስልክ ጮኸ፤ አነሳሁት፡፡ ለካስ እንዲህ በአንዱ አልመልስ ስላት፣ በሌላው እያፈራረቀች
የምትደውለው ዕድሜዋ ወደ ሰባ እየተጠጋ ያለው አሮጊቷ እናቴ ኖራለች፡-
‹‹አቤት! እናቴ››
‹‹ለምንድነው የዚህን ያህል ስልኩ ሲጮኽ የማትመልሰው?›› ቆጣ ብላ ጠየቀችኝ፡፡
‹‹አስቸኳይ ስራ ላይ ስለነበርኩ ነው››
‹‹ኤዲያ! አንተ ደግሞ ሁል ጊዜ ጠብ ለማይል ነገር፣ ችክ ማለት ትወዳለህ››
…በእርግጥ እናቴ እውነቷን ነው! ችክ ያልኩ ቸካካ ነገር ሳልሆን አልቀርም ፡፡
‹‹ልዕልና›› ጋዜጣ ታግዳለች፤ እንደ‹‹ፍትህ›› እና ‹‹አዲስ ታይምስ›› ሁሉ የስርዓቱ የአፈና ሰለባ ሆናለች፤ የሚገርመው ግን መታገዷ
አይደለም፣ የታገደችበት መንገድ እንጂ፡፡ ከዚህ ቀደም ደጋግሜ እንደገለፅኩት አቶ መለስን የተኩት ሰዎች ከእረሱም የባሱ ጭፍን
አምባገነኖች ናቸው፡፡ ማንንም አይፈሩም፡፡ እግዚአብሄርንም ቢሆን ‹‹በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ካልተጠመቅህ አምላክ ሆነ እንድትቀጥል
አንፈቅድልህም›› ከማለት አይመለሱም፡፡
የሆነ ሆኖ የስርዓቱ አይን አውጣነት የደረሰበትን ደረጃ ለመገንዘብ የሚከተለውን በጥሞና አንብቡ፡፡
የ‹‹ልዕልና›› አሳታሚ ድርጅት በሁለት ወዳጆቼ ስም ከተገዛ በኋላ፣ ስም ከመዞሩ በፊት ስርዓቱን ወጥመድ ውስጥ የሚከት ስልት
(አይን ያወጣ አምባገነን ባህሪውን ወዳጆቹ ሳይቀር ይኮንኑት ዘንድ ወደ አደባባይ የሚያወጣ) ተነደፈ፡፡ በስልቱ መሰረትም ከቀድሞ
የድርጅቱ ባለቤቶች ጋር አንድ ስምምነት ተደረገ፡፡ ይኸውም እኔ የሚጠበቅብኝን የአክሲዎን ሽያጭ ክፍያ አስቀድሜ ብከፍልም፤ ምንም
አይነት የስም ዝውውር ሳይደረግ ባለቤትነቱ በእነርሱ ስም ሆኖ እንዲቀጥል ተስማማን፡፡ በዚሁ መንገድ ስራው ተጀመረ፡፡ ለአፈና
ሲንደረደር ግራና ቀኝ ለማያጣራው መንግስት ደግሞ እንዲህ የሚል የ‹‹ተጋገረ›› መረጃ በጋዜጣችን ላይ አስተላለፍን ፡-
‹‹በህጋዊ መንገድ የስም ዝውውር አድርገን ነው ስራ የጀመርነው፡፡››
እነሆ ይህ በሆነ በአስራ ሶስተኛው ቀን (13/07/05) ብሮድካስት ውስጥ ያሉ ዞምቢዎች
‹‹ድርጅቱ ለሌላ ሶስተኛ ወገን በህገ-ወጥ መንገድ የስም ዝውውር አስተላልፏል›› ሲሉ ድምፃቸውን አሰሙ፡፡
መቼ ተላለፈ? የተላለፈላቸው ሰዎችስ ስም ማን ይባላል? የሚሉት መሰረታዊ ጥያቄዎች ብሮድካስትን አያሳስቡትም፤ ያውም አንድ
የሚዲያ ተቋምን ያህል ነገር ሲዘጋ (በነገራችን ላይ የስም ዝውውር የተደረገው ብሮድካስት ደብዳቤውን ከፃፈ ከአምስት ቀን በኋላ
/በ18/07/05/) ነው፡፡
ለብሮድካስት ህገ-ወጥ እግድ ጋዜጣዋ መገዛት እንደሌለባት አዘጋጆቹ ስምምነት ላይ ስለደርሰን በ20/07/05 ታተመች፡፡ ሆኖም ሌላው
ዞምቢ ድምፁን አሰማ-ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፡፡ ይህ መስሪያ ቤት ያለምንም ማጣራት ጋዜጣዋ በወጣችበት ዕለት (20/07/05)
ንግድ ፍቃዳችንን መሰረዙን የሚገልፅ ደብዳቤ ላከልን፡፡ በእጅጉ የሚገርመው ሁለቱም ‹‹ተቋምዎች›› ህገ-ወጥነታችንን የገለፁት
ተመሳሳይ የአዋጅ ቁጥር በመጥቀስ መሆኑ ነው፡፡ ‹‹ከመገናኛ እና ብዙሃን የመረጃ ነፃነት አዋጅ ቁጥር 590/200 ከሚፈቅደው ውጪ…››
በማለት፡፡ …ይህ ምን ማለት ነው? በዚህ አዋጅ ውስጥ በርካታ አንቀፆች ተደንግገዋል፡፡ ስለአታሚ፣ አሳታሚ፣ ዋና አዘጋጅ፣ መረጃ
ተመስገን ደሳለኝየማግኘት መብት፣ የማሳተምና የመደራጀት ነፃነት፣ ስለአከፋፋዮች… አጅግ ብዙ ጉዳዮችን ያካትታል፡፡ ታዲያ እኛ የታገድነው ከእነዚህ
ሁሉ አንቀፆች የትኛውን ተላልፈን ነው? …ቢያንስ መንግስት የሚመስል ነገር ወይም ‹‹መንግስት ነኝ›› የሚል ካለ ጥፋታችንና
የተላለፍነውን የአዋጁን አንቀፅ ቢነግረን ሌላው ቢቀር ከስሜት መጎዳት እንድን ነበር፡፡ ነገር ግትን ዞምቢዎቹ እንደከዚህ ቀደሙ አንቀፅ
በመጥቀስ ማስመሰል እንኳን አልቻሉም፡፡ በደፈናው የአዋጅ ቁጥር ጠቀሱና አረፉት፡፡
…አሁን ሀገራችን አስፈሪ ደረጃ ላይ ደርሳለች፡፡ በአደባባይ ህግ ለመጣስና የፈቀዳቸውን ለማድረግ ትንሽ እንኳ በማያመነቱ አደገኛ ሰዎች
መዳፍ ስር ወድቃለች፡፡ የአማርኛ ቋንቋ ተናገሪዎች ለዓመታት ከሰፈሩበት ቀዬ በኃይል መፈናቀላቸው ቀጥሏል፡፡ በእርግጥ በመለስ
ዘመንም ቢሆን መፈናቀሉ ነበር፡፡ ኧረ እንዲያውም ‹‹ደን እየጨፈጨፉ ስላስቸገሩ ነው›› ብሎ ሁሉ አላግጦባቸዋል፡፡
የአማራው ‹‹ወኪል›› ነኝ የሚለው ብአዴንም ቢሆን ከታምራት ላይኔ ክፉ መንፈስ ገና ነፃ አልወጣም፡፡ ታምራት ላይኔ በስልጣን ዘመኑ
በርካታ የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ተወላጆች በየአካባቢው ሞትና መፈናቀል እየደረሰባቸው እንደሆነ ሲነገረው ‹‹እኛ ከክልል ሶስት ውጪ
ስለሚኖሩ አማሮች አያገባንም፡፡ ምክንያቱም በነፍጠኝነት ለወረራ የሄዱ ናቸው›› ብሎ ተሳለቆ ነበር፡፡ ዛሬ እነኦቦ አዲሱ ለገሰም ከዚህ
አቋማቸው አልተቀየሩም፡፡ ተወልደ ወ/ማርያም በክፍፍሉ ወቅት ብአዴኖች ከመለስ ጎን በመቆማቸው ተበሳጭቶ ‹‹የፖለቲካ ደሀ ናችሁ››
ሲል መተቸቱ በረከት ስምዖን ዛሬም የገባው አይመስለኝም፡፡
የማፈናቀሉ መሀንዲስ ህወሓትም ቢሆን ይህ መንገድ ብዙ ርቀት የማያስኬድ ስለመሆኑ ከሃያ ዓመት በኋላም አልተገለፀለትም፡፡ ለዚህም
ይመስለኛል ከፋፍሎ በመግዛት እና በማዳከም ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ በመከተል ጉልበቱን እያዛለ ያለው፡፡ በነገራችን ላይ መረሳት
የሌለበት ቁም-ነገር የጥፋት ስራው ተጠያቂ ህወሓት እንጂ ‹‹እወክለዋለው›› የሚለው የትግራይ ህዝብ አለመሆኑ ነው፡፡ አማራ-
በብአዴን፣ ኦሮሞ-በኦህዴድ እንደማይገለፀው ሁሉ፣ የትግራይ ህዝብም በህወሓት ይገለፃል የሚል የጨዋታ ህግ የለም፡፡ እነዚህ ሰዎች
ለስልጣናቸው እስከጠቀመ ድረስ የማይፈፅሙት ህገ-ወጥ ድርጊት አለመኖሩ ላይ መስማማት የሚኖርብን ይመስለኛል፤ የማይፈፅሙት
ጭካኔም የለም፡፡ ይህንን የሚያሳይ አንድ ነገር ልንገራችሁ፡፡ ታሪኩ የቀድሞ የደህንነት ሹም የነበረው ክንፈ ገ/መድህንን በጥይት ደብድቦ
ስለገደለው ሻለቃ ፀሀዬን የሚመለከት ነው፡፡ እንደሚታወቀው ሟችም ገዳይም ትግርኛ ተናጋሪዎች ቢሆኑም፣ ሻለቃው ወንጀሉን ከፈፀመ
በኋላ ለብዙ ችግር ተዳርጎ ነበር፣ ያውም ከነቤተሰቡ፡፡ መጀመሪያ ባለቤቱን ከምትሰራበት ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት አባረሯት፡፡ እግር
በእግርም እየተከታተሉ በኪራይ ከምትኖርበት ቤት አፈናቀሏት (በጊዜው እስክንድር ነጋ የገንዘብ ድጋፍ ያደርግላት ነበር) ሻለቃውም
ለስድስት ዓመት ያህል በጨለማ ቤት ውስጥ በመታሰሩ የአይን ብርሃኑ በከፍተኛ ደረጃ ተጎዳ፡፡ ፍርድ ቤት ሲቀርብ እንዴት ለመራመድ
ይቸገር እንደነበረ አስተውለናል፡፡ እኔ እያልኩ ያለሁት ያጠፋ ሰው በህግ አይጠየቅ አይደለም፤ ከህግ ውጪ ስለምን የበቀል ሰለባ ይሆናል
ነው? ሰዎቹ ከየትኛውም ብሄር ተወለዱ በጠላትነት ከመዘገቧችሁ ለጭካኔያቸው ወደር የለውም፡፡
የሆነው ሆኖ ስርዓቱ ገደብ ላጣው ጭካኔው ‹‹ብሄር›› የተሰኘ አጥር የለውም ያስባለኝ በሻለቃው ህይወት መጨረሻ የተፈፀመው ድርጊት
ነውና እሱን ልንገራችሁ፡፡
ዕለቱ የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮች ‹‹ፍልሰታ›› እያሉ የሚጠሩት የአስራ ስድስት ቀን ፆም ዋዜማ ነው-ሐምሌ 30ቀን፡፡
ሻለቃው ይህች ቀን የመጨረሻዋ መሆኗን ሊያውቅ የሚችልበት አገጣሚ አልነበረምና ጥብቅ ሀይማኖተኛ በመሆኑ ለፆሙ የመንፍስና የቁስ
ዝግጅቱን አጠናቆ በደስታ እየጠበቀ ነው፡፡ የሆነው ግን በተቃራኒው ነበር፡፡
በፃሃፊ ብዕር ልተርክላችሁ፡፡
…ወቅቱ ክረምት ቢሆንም ፀሀይ ህቡዕ የገባች እስኪመስል ድረስ ዝናብን አግደው የያዙ የሰማይ መስኮቶች ከንጋት ጀምረው ላንቃቸውን
ከፍተው ምድሪቱን እያረሰረሷት ነው፡፡ ቀኑ ተገባዶ አስር ሰዓት ላይ ደርሷል፡፡ አብዛኛው እስረኛ በየክፍሉ ከቷል፡፡ ጥቂቶቹ ደግሞ
ውሽንፍሩን ተከትሎ ያረበበውን ቅዝቃዜ ይከላከልልናል በሚል ካፍቴሪያ ውስጥ ቁጭ ብለው ሻይና ቡና ደጋግመው ያዛሉ፡፡
አንዲት የደህንነት መኪና ሾፌሩን ጨምሮ አራት ሰዎች አሳፍራ ወደማረሚያ ቤቱ አስተዳደር መግባቷን ማንም አላስተዋለም፡፡ መኪናዋ
የኃላፊውን ቢሮ ታካ ስትቆም የቡድኑ መሪ ቀልጠፍ ብሎ ወርዶ በቀጥታ ከፊቱ ወደአለው ቢሮ በመግባት፣ ከማረሚያ ቤቱ ኃላፊ ጋር
ለጥቂት ደቂቃዎች ቆይታ ከአደረገ በኋላ በወህኒ ቤቱ ውስጥ ያልተለመደ ትዕዛዝ ተላለፈ፤ ሁሉም እስረኛ ወደ ክፍሉ እንዲገባ የሚል፡፡እስረኞቹ በሙሉ ወደ ክፍላቸው መግባታቸው ከተረጋገጠ በኋላ የሞት ፍርድ ተፈርዶበት ቀኑን እየጠበቀ የነበረው ሻለቃ ፀሀዬ
ከክፍሉ ወጥቶ ከደህንነት ቢሮ ወደመጣችው መኪና ውስጥ እንዲገባ ተደረገ፡፡ መኪናዋም በመጣችበት ፍጥነት የመልስ ጉዞ አደረገች፡፡
ይህ ሁሉ ነገር ተካሄዶ ያለቀው በአስራ አምስት ደቂቃ ውስጥ ነበር፡፡
...ጎዳናው ላይ አልፎ አልፎ እየተንገዳገደ ከሚያዘግም ሰካራም እና ከሚያላዝኑ የመንገድ ዳር ውሾች በቀር አንዳች እንቅስቃሴ አይታይም፤
ጭር ብሏል፡፡ የክረምቱ ቅዝቃዜ በድቅድቅ ጨለማ ቁጥጥር ስር ከዋለው ሌሊት ጋር ተቀላቅሎ በእጅጉ ያስፈራል፡፡ የሻለቃው ባለቤት
ወ/ሮ አምሳለ የመኖሪያ ቤቷ በር ሲንኳኳ ከሶስት ልጆቿ ጋር በእንቅልፍ ዓለም ውስጥ ነበረች፡፡ ማንኳኳቱ ሳይቋረጥ ለደቂቃዎች
በመቀጠሉ ድንገት ካሰጠማት እንቅልፍ አባነናት፡፡ እናም በሩን ከፈተች፡፡ ከዚህ ቀደም አይታቸው የማታውቃቸው ሁለት ሰዎች ቆመዋል፡
፡ ደነገጠች፡፡
‹‹ምንድን ነው? ምን ፈልጋችሁ ነው?›› አከታትላ ጠየቀች፡፡
‹‹ፖሊሶች ነን፣ ሻለቃ ፀሀዬ በጣም ስለታመመ አምሳለን ጥሩልኝ ስላለን ነው የመጣነው›› ሲል መለሰ አንደኛው ሰውዬ፡፡
‹‹ቀን ስንቅ ስወስድለት ደህና አልነበረ እንዴ? አሁን ምን ተፈጠረ?››
‹‹ድንገት ነው የታመመው፤ ልታዪው የምትፈልጊ ከሆነ ቶሎ እንሂድ?›› አለና አጣደፋት በሌሊት ከሰው ደጅ ቆሞ መመላለሱ
ያልተመቸው ሁለተኛው ሰው፡፡ ወ/ሮ አምሳለም ስጋት እንደሞላት ሰዎቹን አሳፍራ በመጣችው መኪና ውስጥ ገብች፡፡ ሆኖም መኪናዋ
ወደመጣችበት መመለሰ ስትጀምር መንገዱ ወደቃሊቲ የሚወስደው እንዳልሆነ ተረዳች፡፡ ከሃያ ደቂቃ ጉዞ በኋላም መኪናዋ አንድ ግቢ
ውስጥ ገብታ ቆመች፡፡ ሁሉም ወረዱ፡፡
‹‹የታለ ባለቤቴ?›› አምሳለ ጠየቀች፣
‹‹ያው! እዛ ክፍል ውስጥ ግቢ፣ እየጠበቀሽ ነው›› አላት አንደኛው ሰው፣ በሩ ወደተከፈተ ክፍል በእጁ እያመለከተ፡፡
እንደተባለችው ገርበብ የተደረገውን በር ሙሉ በሙሉ ከፍታ ገባች፡፡ …ክፍሉ ወለል መሀል ላይ ሻለቃው በጥይት ተበሳስቶ በጀርባው
ተዘርሯል፡፡ …ያልጠበቀችውን ክስተት የተመለከተችው የሻለቃው ባለቤት እንደሎጥ ሚስት የጨው አምድ ሆነች፡፡ …የዚህን ያህል ነው
የህወሓት ጭካኔ፡፡ ከመስመሩ ካፈነገጣችሁ ትግሬ ሆናችሁ አማራ ጉዳዩ አይደለም፡፡ እናም ማቆሚያ ላጣው የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች
መፈናቀልም ብቸኛው ተጠያቂ ህወሓት እንጂ ‹‹ወከልኩት›› የሚለው ህዝብ በፍፁም ሊሆን አይችልም፡፡ ይህ አመለካከት የተሳሳተ
ከመሆኑም በላይ የማይታረም አደጋ ያስከትላል፡፡
የሆነ ሆኖ እንዲህ አይነቱን አጓጉል ችግር ፈጣሪ ድርጊት ሁላችንም በጋራ ለማስቆም መሰለፍ አለብን፡፡ በይበልጥ ደግሞ ከሀገሪቱ የተለያዩ
አካባባዎች መጥታችሁ፣ የተለያየ አካባቢ ሰፍራችሁ ሀብት እያፈራችሁ ያላችሁ ኢትዮጵያውያን ነጋዴዎች ይህ አይነቱ ማፈናቀል ባስቸኳይ
ይቆም ዘንድ ነግ በእኔ ብላችሁ ስርዓቱ ላይ ጫና ማሳደር አለባችሁ፡፡ ቀጣዩ ተረኛ እናንተ ላለመሆናችሁ ምንም ማረጋገጫ የለም፡፡
የስርዓቱ ደጋፊዎችም ሆናችሁ ልሂቃኖች፣ በአሰልቺ ዜማ ጠዋትና ማታ ‹‹አባይ፣ አባይ…›› የምትሉ አርቲስቶች ከምንም በፊት ስለንፁሀን
እምባ መገደብ ልትናገሩ ይገባል፡፡ አገዛዙ የዱርዬ ባህሪውን ይገድብ ዘንድ ስትዘምሩ መስማት እንፈልጋለን፡፡ … እስቲ ዙሪያችንን
እንመልከት፤ ትላንት ከኋላችው ቆምን ነፃ ያወጣናቸው ሀገራት ዛሬ የብሄር ፖለቲካን ለእኛ ጥለውልን ርቀው ሄደዋል፡፡ በዘላቂነት አብሮን
ለማይቆይና ጠብ ለማይል ነገር እንማስናለን፡፡ እናቴም እንዲሁ ነበር ያለችኝ ‹‹ችክ አትበል! ጠብ ለማይል ነገር!›› ሆኖም ግሳጼዋን ችላ
ብዬ ለምን እንደደወለችልኝ ጠየኳት፡፡
‹‹ትላንት ለምን ወደ ቤት አልመጣህም?››
‹‹ምነው ፈልገሽኝ ነበር እንዴ?››
‹‹አዎ! የአባትህ 13ኛ ሙት ዓመት ነበር እኮ›› …ደነገጥኩ፡፡ ጊዜው እንዴት ይሮጣል? ግና በለሆሳስ ‹‹አባቴ ሆይ ነፍስህ በአፀደ ገነት
እንዳለች አምናለሁ!›› ስል እናቴ ማነብነቤን ሰምታኝ ኖሮ ምን እንዳልኩ ጠየቀችኝ፡፡‹‹አይ! ምንም አላልኩም››
‹‹ለማንኛውም ዛሬ ወደ ቤት እንድትመጣ?››
‹‹እናቴ! ቢሮ ስለማመሽ ልመጣ አልችልም፤ ራሴ ቤት ነው የማድረው››
‹‹እረስተከዋል እንዴ! ዛሬ እኮ መጋቢት ሀያ ሰባት ነው››
‹‹እና ታዲያ?››
‹‹የተወለድክበት ቀን ነዋ!›› …ሌላ የተረሳ ጉዳይ፡፡ ይህ ሳምንት ድብልቅልቅ ያለ ነው፡፡ የአባቴ 13ኛ ሙት ዓመት፣ የልደት ቀን፣ ሽልማት
(በነገራችን ላይ ‹‹ኢትዮቲዩብ›› ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትን ለማስከበር አስተዋፆ አድርገሀል በማለት የሸለመው እኔን ብቻ ሳይሆን
ባልደረቦቼንና አንባብያንንም ጭምር በመሆኑ በሁሉም ስም እንዲህ ማመስገኑ አስፈላጊ ሆኖ አግኝቸዋለው፡- ‹‹እንዳከበራችሁን
እግዚአብሄር ያክብርልን፤ መጪውም ከዚህ የበለጠ ስራ የምትሰሩበት የስኬት ዘመን ይሆንላችሁ ዘንድ እመኛለሁ››)
ይህንን ርዕሰ ጉዳይ ከማሳረጌ በፊት መልዕክቴን ላስተላልፍ፡-
አሁንም ትግሉ ይቀጥላል፡፡ ‹‹ልዕልና›› ብትዘጋም ሌላ ይከፈታል፡፡ ትግል… ሽንፈት፤ …ድል፤ እንደገና መሸነፍ… ተስፋ አንቆረጥም፤ ገና
ወደፊት እንቀጥላለን፤ በዘመናችን ብዙ ነገር አይተናል፤ ርዕዮተ-ዓለም ሲሸነፍ ተመልከተናል፤ ስርዓት ድል ሲመታ አይተናል፤ ህዝብ እንደ
ህዝብ ሲሸነፍ ግን ማንም ተመልክቶ አያውቅም፡፡ እናም እኔ ጋዜጠኛ ነኝ ‹‹ለዲሞክራሲና መልካም አስተዳደር ፀልዩ›› ብዬ ልመክር
አልችልም፡፡ ነገር ግን እልፍ ሆነን እንዘምር ዘንድ ድምፄን ከፍ አድርጌ እጠይቃለሁ፡-
አትነሳም ወይ? አትነሳም ወይ?
ይሄ ባንዲራ የአንተ አይደለም ወይ?
…ኢ-ፍታሀዊነትን እንዋጋለን፣ የከፋፍለህ ግዛን አስተዳደር እንቀይራለን፡፡ በሩንም በሰላም ይከፍቱልን ዘንድ ደጋግመን እናንኳኳለን፤
ካልከፈቱልንም ገንጥለን እንገባለን፡፡ ከዛ በኋላም ሀገራችንን የራሳችን እናደርጋለን! ያዘኑትም ይስቃሉ፤ የታሰሩትም ይፈታሉ፤
የተሰደዱትም ይመለሳሉ፤ የወጡትም ይወርዳሉ፡፡
(መጋቢት 27/2005 ዓ.ም እኩለ ሌሊት)

ዳምጠው ወያኔ/ኢሕአዴግና አፈና በኢትዮጵያ


ዳምጠው ወያኔ/ኢሕአዴግና አፈና በኢትዮጵያ

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም
መጋቢት 2005
በቀልድ ልጀምር፤ አንድ ጮሌ የአስመራ ልጅ የእኔ ተማሪ ነበር፤ አንድ ጊዜ የጂኦግራፊ ክፍል ተማሪዎች አንድ ጃፓናዊ አስተማሪ ለመሸኘት ግብዣ አድርገው ነበር፤ በግብዣው ላይProfessor Mesfin Woldemariam is one of Ethiopia's well-known intellectuals የጠቀስሁት ነገረኛ የአስመራ ልጅ (የአስመራ ልጅ የምለው ላርቀው ፈልጌ እንዳይመስላችሁ፤) በአስተማሪዎች ላይ ቀልድ ያሰማ ነበረ፤ ስለኔ ሲናገር፤– መስፍን ወልደ ማርያም የቢሮውን በር ሁልጊዜ ክፍት አድርጎ የሚቀመጠው ለምንድን ነው? ይልና እሱው ሲመልስ፣ በሩን የመዝጋት ሌሎች ዘዴዎች ስላሉ ነዋ! ቀልዱ ለእኔ እንደገባኝ ፊቱን ስለሚያኮሳትር ሰዎች በሩን አልፈው እንዲገቡ አይጋብዝም ማለት ነው፤ በዚያን ጊዜ እኔም እየሳቅሁ እንደተናገርሁት የሱን ፈሪነት በእኔ መልከ-ክፉነት መደበቁ ነው፤ ቀልዱን ያመጣሁበት ምክንያት ወያኔ ለነጻነት የቆመ መስሎ ለመታየት ሳንሱር የሚባለውን የሚታተሙ ጽሑፎችን በቅድሚያ የማስፈተሽ ቀንበር በሕግ አነሣ፤ ሰዎች እውነት መስሎአቸው ቅሪታቸውን እያነጠፉ ጋዜጦችና መጽሔቶችን ማሳተም ጀመሩ፤ ጋዜጦች እንደአሸን ፈሉ፤ መጻሕፍት ታተሙ፤ ጥቂት ቲያትሮችም ታዩ፤ ዘፈኖች ተመረቱ! ነገር ግን የግል ራድዮና ቴሌቪዥን እንዲሁ የብዙ ሰዎች ሕልም ሆኖ ቀረ፤ ብዙ ሰዎች ብዙ ገንዘብ ከሰሩ፡፡
በሕዝቡ ዘንድ የነጻነት ፍቅር እየለመለመ መሄዱን ሲያየው ወያኔ ሆዱ ተንቦጨቦጨ፤ እንቅልፍ እያጣ ሄደ፤ ቀስ በቀስ ግራ እጁን በሕገ መንግሥቱ ላይ ጭኖ በቀኝ እጁ ጎራዴውን መዘዘ፤ ቀስ በቀስ፣ አንድ በአንድ የተለያዩ መብቶችን ለማስከበር የቆሙትን አንቀጾች ሁሉ አስተኛቸው፤ በተገላቢጦሽ መብቶቻቸውን የሚጠይቁ ሰዎችን፣ ስለመብቶች የሚጽፉ ሰዎችን፣ መብቶችን ከጥቃት ለመከላለከል የቆሙ ድርጅቶችን፣ ከወያኔ አመለካከት ውጭ የሆኑ ሰዎችን ሁሉ መንግሥት በመገልበጥ ሴራ፣ ወይም በሽብርተኛነት እየያዘና እያሰረ በመክሰስና በማስፈረድ የማፈን እርምጃዎችን ሁሉ አጠናከረ፤ አንዲህ ያለውን አፈና ማየትና መስማት እየተለመደ መጣ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ በሽብር ስም የሚካሄደው ጥቃትና የሰብአዊ መብቶች ረገጣ እንኳን እኛንና በሽብር ላይ ዓለም-አቀፍ ጦርነት ያወጁትን አሜሪካኖችንም እያስደነገጠ ነው፤ የዓለም የሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች ሁሉ፣ የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንን ጨምሮ በምሬት እየጮሁ ነው፤ ጋዜጠኞች፣ የሠራተኞች ማኅበሮች፣ የፖሊቲካ ቡድኖች ጭጭ እንዲሉና ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ መንገዱ ሁሉ እየተዘጋባቸው ነው፤ በትግራይ አብርሃ ደስታ የሚባል ወጣት የአፈናውን ድቅድቅ ጨለማ ጥሶ በመውጣት ስለጻፈ አፈናና ማስፈራራት ደረሰበት፤ ‹‹ጭቆናን ስላጋለጥሁ የሕዝብ ጠላት ተባልሁ›› ይላል፤ በቅርቡ እንኳን ሰማያዊ ፓርቲ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል የጠራው የራት ግብዣ እንግዶቹ በተጠሩበት ሰዓት ተሰርዞ ተመልሰዋል፤ ለግራዚያኒ ስለሚሠራው ሐውልት የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ የሞከሩ ኢትዮጵያውያን ታሰሩ፤ እነዚህን ኢትዮጵያውያንን ያሰሩትን ምን እንላቸዋለን? እንግዲህ በኢትዮጵያ ውስጥ ምን የማያሳስር ነገር ሊኖር ይችላል?
የአፈናውን ነገር እነእስክንድር ነጋ፣ እነርእዮት ዓለሙ፣ ውብሸት ታየ … ይመሰክራሉ፤ ለመሆኑ ወደዘጠና ሚልዮን የሚሆን ሕዝብ ያላት አገር ስንት ጋዜጣ፣ ስንት የራድዮ ጣቢያ፣ ስንት የቴሌቪዥን ጣቢያ አላት? ኤርትራ ሦስት የራድዮ ጣቢያዎችና ስድስት ጋዜጦች፣ ጂቡቲ ሦስት የራድዮ ጣቢያዎችና አምስት ጋዜጦች፣ ኬንያ አሥራ ስምንት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች፣ ከሠላሳ በላይ የራድዮ ጣቢያዎች፣ ዘጠኝ ጋዜጦች አሉት፤ ትናንት የተፈጠረው ደቡብ ሱዳን እንኳን ሁለት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች፣ አምስት የራድዮ ጣቢያዎች፣ አምስት ጋዜጦች አሉት፤ ኢትዮጵያ ያላትን እናውቃለን፡፡
ሰንጠረጅ አንድ
የኪስ ስልክ (ሞባይል) እድገት
እ.አ.አ.2008200920102011
አገሮችሞባይል ለ100 ሰዎች
በደቡብአፍ
91
93
100
127
ኢትዮጵያ
2
5
8
17
ኬንያ
42
49
62
65
ሱዳን
29
36
42
56
ኤርትራ
2
3
4
4
ሶማልያ
7
7
7
7
ጂቡቲ
13
15
19
21
ምንጭ፡- የዓለም ባንክና የዓለም ቴሌኮሚዩኒኬሽን ድርጅት
የአፈናውን ልክ በሁለቱ ሰንጠረጆች ማየት ይቻላል፤ ለንጽጽር የቀረቡት አገሮች የአፍሪካ ቀንድ ጎረቤቶች ናቸው፤ ነገር ግን ላቅ ያለ ግብ ለማመልከት ደቡብ አፍሪካ ተጨምሮአል፤ ለምሳሌ የኪስ ስልኩን ብንወስድ በደቡብ አፍሪካ በመጀመሪያው ዓመት እአአ በ2008 ለአንድ መቶ ሰዎች 91 የኪስ ሰልኮች ነበሩ በ2011 ለመቶ ሰዎች ወደ አንድ መቶ ሃያ ሰባት ደረሱ፤ ይህም አንዳንድ ሰዎች ከአንድ በላይ የኪስ ስልክ አላቸው ማለት ነው፤ከጎረቤቶቻችን መሀል ኬንያ በ42 የኪስ ስልኮች ለአንድ መቶ ሰዎች ጀምሮ በአራተኛው ዓመት ላይ ወደስድሳ አምስት ማደጉ ይታያል፤ ሱዳንም ከሃያ ዘጠኝ ተነሥቶ በአራተኛው ዓመት ወደሃምሳ ስድስት አድጎአል፤ ጂቡቲም ከ13 ጀምራ ወደ 21 ገብታለች፤ ትልቅዋ አገር ኢትዮጵያ በሁለት ጀምራ ከአራት ዓመታት በኋላ ለመቶ ሰዎች አሥራ ሰባት የኪስ ስልኮች አስቆጥራለች፤ በአፍሪካ ቀንድ በኪስ ስልክ የመጨረሻውን ዝቅተኛ ቦታ የያዘች አገር ትልቅዋና በዓመት ከአሥራ አንድ ከመቶ በላይ እድገት ታስመዘግባለች የሚባልላት ኢትዮጵያ ነች፡፡
ሁለተኛው የአፈናው መገለጫ የኢንተርኔት አገልግሎት ነው፤ በኬንያ በ2008 ከአንድ መቶ ሰዎች ውስጥ የኢንተርኔት ተጠቃሚ የነበረው 42 ሲሆን በ2011 ወደ ስድሳ አምስት አደገ፤ በኤርትራ ከ4 ወደ 6 ሲያድግ፣ በኢትዮጵያ አላደገም፡፡
እነዚህ ሁለቱም የመረጃና የእውቀት መተላለፊያ ዘዴዎች ለማናቸውም እድገት ቁልፍ መሆናቸው አያጠራጥርም፤ በተለይም ለነጻነትና ለእውቀት እድገት አስፈላጊዎች በመሆናቸው ለአምባ-ገነኖች እንደጠላት መሣሪያ የሚቆጠሩ ናቸው፤ ችግሩ እውቀት አለነጻነት አይገኝም፤ ነጻነትም አለእውቀት አይገኝም፤ እውቀትና ነጻነት ተነጣጥለው አይገኙም፤ ስለዚህም ነጻነትን ለመግደል የፈለገ እውቀትንም ይገድላል፤ ስለዚህም አምባ-ገነኖች ሞባይልንና (ተንቀሳቃሽ ወይም የኪስ ስልክ) ኢንተርኔትን ማፈን ዋና ተግባራቸው ያደርጉታል፤ በዚህም ምክንያት ሕዝቦቻቸውን በድንቁርና ያዳፍናሉ፤ በደሀነት ያሰቃያሉ፤ በዘመናችን ዋናው የአውቀት መተላለፊያ ኢንተርኔት ነው፡፡
ሰንጠረጅ ሁለት
የኢንተርኔት አገልግሎት እድገት
   
እ.አ.አ.2008200920102011
አገሮችየኢንተርኔት አገልግሎት ለመቶ ሰዎች
ደቡብአፍ8.510.118.120.9
ኢትዮጵያ0.50.50.81.1
ሱዳን10.2   
ኤርትራ4.14.95.46.2
ሶማልያ1.11.21.3
ጂቡቲ2.34.06.57.0
ደቡብ አፍሪካ የገባው ለንጽጽር ነው፤
ምንጭ፡- የዓለም ባንክና የዓለም የቴሌኮሚዩኒኬሽን ድርጅት
የኢንተርኔት አገልግሎት በቅርቡና በርካሽ ወይም በነጻ ከተገኘ ብዙ ሳይለፉ ምንም ዓይነት እውቀት ሊገኝ ይቻላል፤ በሠለጠኑት አገሮች በአንዳንድ ቡና ቤቶች ነጻ የኢንተርኔት አገልግሎት ይገኛል፤ በኢትዮጵያ ውስጥ በኢንተርኔት ለመጠቀም ደህና ገቢ ያለው መሆን ያስፈልጋል፤ከደሀነት ለመውጣትም ሀብታም መሆን ያስፈልጋል!

የሲፒጄውን ተሸላሚ” ዳዊት ከበደን መጨረሻ ማየት ናፈቀኝ

የሲፒጄውን ተሸላሚ” ዳዊት ከበደን መጨረሻ ማየት ናፈቀኝ

ክፈሌ ስንሻው አኔሳ
ዳዊት ከበደ ያለተቀናቃኝ አውራምባ ታይምስ የተባለ ጋዜጣን ሲያስትም ቆየ። እንደ ዳዊት ለ2 አመታት ታስረው የተፈቱት ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና እና እስክንድር ነጋ የጋዜጣ
Journalist Dawit Kebede, Awramba Times editor
ከፌስ-ቡክ የተገኘ
ህትመት ፈቃድ ተከልክለው ለእሱ  ተፈቀደ። ለምን ለእሱ ተፈቀደ ብሎ የጠየቀ አልነበረም፤ በእስር ቤት ተፈትኖ የወጣ በመሆኑ ለወያኔ ያድራል ብሎ የሚጠረጥር  ሰው አልነበረምና። ዳዊት  አውራምባን ማሳተም ቀጠለ። ጋዜጣው ጥሩ ስራ እየሰራ ባለበት ጊዜ ዋና አዘጋጁ “ልጁን አላምነውም ብሎ” ጥሎት ጠፋ። ዋና አዘጋጁ በወቅቱ ይናገር የነበረውን ማንም አላመነውም ነበር፤ ቀጥሎም ተረበኛው አቤ ቶክቾው ድርጅቱን ለቀቀ።
አውራምባም፣  ሄደች ሄደችና  ገበያዋ ሲደራ፣ መሀል መንገድ  ቀረች ቆማ ተገትራ ተባለች፤ “ጠንካራ ዘገባዎችን” ማውጣት አቆመች፣ ዜናዎቿ ሁሉ ” ጁነዲን ምሳ በላ፣ አባዱላ ውቅሮን ጎበኘ” ወዘተ ሆነ ። “ዳዊት ከበደ መፍራት ጀምሯል” ተብሎ በአዲስ አበባ መወራት ጀመረ፤ በመሀሉ ሲፒጄ የሚባል ድርጅት የአመቱ ምርጥ ሰው አድርጎ ሸለመው፤ የዳዊትም ስም እንደገና  ከፍ ከፍ አለ። ሁላችንም ዳዊት በመሸለሙ (የመጀመሪያው የሲፒጄ ኢትዮጵያዊ ተሸላሚ በመሆኑም) ደስ አለን፤ እኔ በግሌ በጣም ተደሰትኩ። ዳዊት ግን አንድ ፈተና ገጠመው- በአገር ቤት። ዳዊት ሽልማቱን ለመውሰድ እዚህ አሜሪካ ሲመጣ መቀናጣት አበዛና ስራውን ዘነጋው። በአሜሪካ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ የሰጠውን ድጋፍ ሲመለከት  “ፕሬዚዳንት ኦባማን” የሆነ መሰለው። ስራውን ትቶም አሜሪካ ማውደልደል ጀመረ። እናም በአገር ቤት፣  አንድ ተመስገን ደሳለኝ የተባለ ጋዜጠኛ “ፍትህ” የሚባል ጋዜጣ አዘጋጅቶ ዳዊት እየፈራ የማያወጣቸውን ዘገባዎች እያተመ ማውጣት ጀመረ። ሁሉም ፊቱን ከዳዊት ወደ ተመስገን አዞረ፤ አውራምባ ወደቀች፤ ኪሳራ ውስጥም ገባች፤ ዳዊትም “ወያኔ አስፈራራኝ” አለና ከአገር ኮበለለ። እንዴት እንደወጣ እግዚአብሄር ይወቅለት፤ ራሱን ወደ እስር ቤት በመወርወር፣ ሲፒጄ የሰጠውን ሽልማት ትክክል ነው በማስባል፣ ለሲፒጄም መኩሪያ ይሆናል ስንል፣ እነ እስክንድርን ነጋን ወይኒ ሸኝቶልን መጣ።
አሜሪካ ላይ መንጎማለል ያለመው ዳዊት በኢሳት ላይ ቀርቦ መግለጫ ሰጠ፤ እኛም ሰምተን፣ በሆዳችን ሲፒጄን እንዳዋረደ ቢገባንም፣ እዚህም ሆኖ ከታገለ አንድ ነገር ነው ብለን ድጋፋችንን ሰጠነው። ኢሳት ልጁን በተደጋጋሚ በማቅረቡም፣ ኢሳትን አምነን አውራምባ ታይምስ ድረ-ገጽን ሲጀመር፣ ድረገጹን እየከፈትን በማንበብ በገንዘብ እራሱን እንዲደጉም እገዛ ማድረግ ጀመርን።
ዳዊት እንዳለመው በአሜሪካ እንኳንስ “ኦባማ”ን ሊሆን ቀርቶ፣ አንድ ተራ ሰው መሆን አቃተው፣ በምን ምክንያት እንደሆን አይታወቅም እነ ኢትዮ-ሚዲያን መጥላት ጀመረ። ትንሽ ቆይቶም በኢሳት ላይ ዘመቻ ጀመረ፤ “እንዴት ሰው የበላበትን ወጪት ይሰብራል?” ብለን አይተን እንዳላየን አለፍነው። ኢሳት አሳድጎት፣ ኢሳት አስተዋውቆት፣ በኢሳት ላይ መዞሩ በጤናው ነው ስንል ጠየቅን፤ ኢትዮሚዲያስ ቢሆን ስንት ክብር ሰጠው? ቀጠለና አቤ ቶክቾውን በፓልቶክ  ቀጠቀጠው። ይህ ሲገርመኝ እንደ “ፋና ወጊ” የማየውን አርበኛውን ታማኝ በየነን መነካካት ጀመረ፤ የት ይደርሳል የተባለ ዛፍ ቀበሌ ቆረጠው ሆነ ነገሩ። እኔም  ሲፒጄን፣  ኢሳትን፣  ኢትዮሚዲያን መርገም ጀመርኩ፣ አይጥ የሆነውን ልጅ አንበሳ አድርገው በማቅረባቸው። “እኛንም ጎዱን፣ እሱንም ጎዱት”። አንድ ሰው የማይገባውን ክብር ሲያገኝ መሸከም ያቅተዋል፤ ዳዊት ላይ የታየውም ይህ ነው። ሽልማቱ ለሲሳይ ወይ ለእስክንድር ቢሰጥ ኖሮ እነሱ አያያዙን ያውቁበት ነበር፤ ሲሳይ የፔን ኢንተርናሽናል ተሸላሚ ነው፣ እስክንድርም እንዲሁ፤ ሁለቱም ግን እንደ ዳዊት አልፎለሉም፤ ወይም ልታይ ልታይ አላሉም፤ የበለጠ ለመስራት የበለጠ መስዋትነት ለመክፈል ተዘጋጁ እንጅ።
ከስንት ጊዜ በሁዋላ ዛሬ አንዱ ደውሎ “አውራምባን አየኸው” አለኝ?  “ዌብሳይቱ አለ እንዴ? ብየ መለስኩለት። “በኢሳት ላይ የሰራውን ተመልከተው” አለኝ።  ተመለከትኩት። ይህን የሰራው  የሲፒጄው ተሸላሚ ዳዊት ነው? ብየ ራሴን ጠየቅሁ። ዘገባው በ59 የአማራ ተወላጆች ላይ ስለደረሰው አደጋ ነው፤ የአሜሪካ ድምጽ ዘጋቢ ትዝታ በላቸው፣ አንድ ዘገባ አቅርባ ነበር፤ “ኢሳት የዘገበው ትክክል አይደለም” ለማለት ፣ ጋዜጠኞች እንደሚሉት “ለማስተባበል” የፈለገችች ይመስላል፤ ኢሳትም የማስተባበያው ማስተባበያ ዜና ለመስራት የፈለገ ይመስላል። ኢሳት፣ የትዝታን ዘገባ ካቀረበ በሁዋላ የራሱን ሰው አቅርቦ አሰማ፤ የቪኦኤም የኢሳትም ያልሆነው ዳዊት ከበደ  የኢሳትን ግማሹን ዜና በመቁረጥ (ገበሬው የሚናገሩትን) ትዝታ የምትናገርበትን ክፍል ብቻ በማቅረብ ኢሳትን ለመወንጀል ሲሞክር ይታያል፤ የኢሳት ዜና ስሜት የሚሰጠው ገበሬው የሚናገሩበት ክፍል ሲገባ ነው። ዳዊት ግን ያንን ክፍል ሆን ብሎ ቆረጠው። ዳዊት ቢዘቅጥ ቢዘቅጥ በዚህ ደረጃ ይዘቅጣል ብየ አላስብም ነበር፤ ወይ የሲፒጄው ተሸላሚ!
ይህንን በማስመልከት በድረገጹ ላይ ከታች አንድ አስተያየት ጻፍኩ። ዳዊት የሚጋለጥ መሆኑ ሲገባው ወዲያው ጽሁፌን አነሳው። አሁን ይህንን የጉድ ጋዜጠኛ ስራ ታዩት ዘንድ የእሱን ሊንክ እና እውነተኛውን ዜና አያይዤ አቀርባለሁ፤ ፍርዱን ለናንተው ልተወው።
ምንአለበት እንዲህ ፣ እንደ ኢቲቪ፣ የዘቀጠ ስራ ሰርቶ ራሱን ከሚያዋርድ ፣ ትንሽ ስለ አማራ ተፈናቃዮች ዘገባ ቢሰራ።