Saturday, September 29, 2012

‹‹ተቃዋሚ ፓርቲዎች በመሰባሰብ ትልቅ ጉልበት መፍጠር አለባቸው›› አንዱዓለም አራጌ


አንድት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አንዱዓለም አራጌን ጠየቀ
‹‹ተቃዋሚ ፓርቲዎች በመሰባሰብ ትልቅ ጉልበት መፍጠር አለባቸው››
አንዱዓለም አራጌ
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ከፍተኛ አመራሮች መስከረም 17 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም በሽብርተኝነት ስም ታስሮ የሚገኘውንና እና የፓርቲው ከፍተኛ አመራር የሆነውን አቶ አንዱዓለም አራጌን ቃሊቲ በመገኘት ከብዙ ጭቅጭቅ በኋላ በአካል በመገኘትና ለመጠየት በቅቷል፡፡ አመራሩ በተጨማሪም የአንድነት ፓርቲ የብሔራዊ ም/ቤት አባል የሆነውንና ቂሊንጦ ታስሮ የሚኘውን አቶ ናትናኤል መኮንንም እንደጠየቀ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ገልጿል፡፡
የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት አያይዞ እንደገለጠው የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አካላት፣ አባላትና ደጋፊዎች ባለፈው አንድ አመት አንዱዓለምንና ሌሎች የፖለቲካ እስረኞችን ለመጠየቅ ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርጉም ለመጠየቅ ከተመዘገቡ ጥቂት ቤተሰቦች በስተቀር መጠየቅ ሳይቻል ቀርቷል፡፡
በተደጋጋሚ በተደረገው ሙከራ ተስፋ ባለመቁረጥና ሀገ መንግሥታዊ መብትን በመጠቀም የመስቀል በዓል ቀን የአንድነት ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ አባላትና ከብሔራዊ ም/ቤት አባላት የተውጣጡ ሰዎች አቶ አንዱዓለም አራጌንና አቶ ናትናኤል መኮንን ለመጠየቅ ተንቀሳቅሰዋል፡፡
ከከፍተኛ አመራሮች መካከል ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ አቶ አስራት ጣሴ፣ ኢ/ር ዘለቀ ረዲ፣ አቶ ሙላት ጣሰው፣ አቶ ተክሌ በቀለ፣ አቶ ሽመልስ ሀብቴ፣ አቶ ደምሴ መንግሥቱና ሌሎችም የብሔራዊ ምክር ቤት አባላትና የፓርቲው የምክር ቤት ሰብሳቢና ፀሐፊም ተገኝተዋል፡፡ በአጠቃላይ ከ15 በላይ የሚሆኑ ጠያቂዎች ከጠዋቱ 2፡ዐዐ ሰዓት ጀምሮ ቃሊቲ ከተሰባሰቡ በኋላ እንደሌሎች ጠያቂዎች መግባት ሳይፈቀድላቸው ቀርቷል፡፡ የእለቱ ተረኛ ጠባቂዎች ስልክ ከተደዋወሉ በኋላ ‹‹በ6 ሰዓት ኑ ትገባላችሁ›› በማለት መልሰዋቸዋል፡፡ የአንድነት ልዑካንም ተስፋ በማድረግ በጽናት እዚያው የጠበቁ ሲሆን 6 ሰዓት እስከሚሆን በዶ/ር ነገሶ የተመራ ቡድን ቅሊንጦ ወደሚገኘው ናትናኤል መኮንን ጋር በማምራት ከብዙ ንትርክ በኋላ ጠይቀው መለሳቸውን የህዝብ ግንኙነት አስታውቆአል፡፡
በተባለው ሰዓት መሰረት ወደ እስር ቤቱ የደረሱት አመራሮች ለመግባት ቢሞክሩም ‹‹ከተመዘገቡ ሰዎች ውጭ መግባት አይፈቀድም›› በማለት ተከልክለዋል፡፡ የያዙት ምግብ መግባት ቢችልም የመልካም ምኞት መግለጫ የሆኑ ፖስትካርዶች መልእክታቸው እየተነበበ አብዛኞቹ እንዳይገቡ ተደርገዋል፡፡ አብዛኞች የተመለሱት የሚያጽናኑ ጠንካራ ቃላትን የያዙና አንዱዓለምን እንደጀግና የሚቆጥሩ መልእክቶች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
እንዳይገቡ የተከለከሉ የአመራር አባላት የማረሚያ ቤቱን አስተዳዳሪዎች በማግኘት ‹‹ለምን ህገ መንግሥታዊ መብታችን አይከበርም? ታሳሪዎችን የመጠየቅ መብትስ ለምን ይገፈፋል?›› ብለው በጽናት በመጠየቅ በመጨረሻ እንዲገቡ ተፈቅዶላቸው አንዱዓለም አራጌን ከአንድ ዓመት በኋላ ፊት ለፊት አግኝተው ለመጋገር መቻላቸውን የህዝብ ግንኙነት መረጃ ይጠቁማል፡፡
የፓርቲው አመራሮች ዙሪያውን በከበቡ ጠባቂዎች መካከልም ቢሆን አንዳንድ ቁምነገሮችን ለመጫወት ችለዋል፡፡ ከፍተኛ የመንፈስ ጥንካሬና የሞራል ልዕልና የሚታይበት አንዱዓለም ለከፍተኛ አመራሩ ‹‹በማንም ላይ ክፉ ነገር ለማድረግ አስቦ እንደማያውቅና ፍፁም ነፃነት እንደሚሰማው›› የተናገረ ሲሆን የአንድነት አመራሮችም ከጎኑ በመሆን ከዚህ በፊት እኔ ወደ ፍርድ ቤት ለመሄድ እንደማልፈልግ ገልጨ ፓርቲው ግን ወደ ፍርድ ቤት በሄድና መከራከሩ ቢያንስ ለታሪክ እንኩዋን ይጠቅማል በማለት መሄዱ አስፈላጊ መሆኑን በማመኑና እኔንም በማሳመን እንድከራከር በማድረጉ ጥሩ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ አሁንም ፓርቲዬ ይግባኝ እንዲጠየቅና ክርክርሩ እንዲቀልጥ በስራ አስፈፃሚው በመወሰኑ እኔም ይኸው ይግባኝ እንዲጀመር ተስማምቻለሁ፡፡ በአጠቃላይም ለፓርቲዬ አመራር ከፍተኛ ምስጋናም አቀርባለሁ ብሎአል፡፡
አንዱዓለም ‹‹ትግሉን አጠናክሮ ከመቀጠል ውጭ ምርጫ እንደሌለና የተበታተኑ ተቃዋሚዎች በመሰባሰብ ጠንካራ ኃይል ቢፈጥሩ እንደሚጠቅም ተናግሮ የእሱም አላማ ለሁሉም የሆነች ኢትዮጵያን መፍጠር እንጅ ሌላ እንዳልሆነ ገልጿል፡፡››
አመራሩም ምንጊዜም ከጎኑ እንደሆኑና ትግሉንም ግቡን እስከሚመታ አጠንክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጦለታል፡፡
የአንድነት ፓርቲ ዋና ፀሐፊ አቶ አስራት ጣሴ እንደተናገሩት ‹‹እንድንገባ የተደረገው አስበውበት ከሆነ ጥሩ ነው፤ ወደፊትም እንዲፈቱ መጠየቃችንና ከጎናቸው መሆናችንን አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡ አሁን ግን እንድንገባ የተደረገው በድንገት ነው ወይስ ታሶቦበት? የሚለውን ለመመለስ በተከታታይ በመጠየቅ ማረጋገጥ ይኖርብናል›› ብለዋል፡፡

Ethiopia: Hailemariam Desalegn Unwelcome in New York City


by Tedla Asfaw
(New York) The rainy cloudy Sept. 28, 2012 was not a welcome weather for anyone. It was raining hard from earlyHailemariam Desalegn Unwelcome in New York Citymorning and we followed the weather hour by hour fearing for a washout of our rally scheduled for 3pm at 47 Street and 2nd Avenue at UN. Rain started to tamper down at noon but still the cloud was threatening. Hailemariam Desalegnthe new Ethiopian PM, might have liked the rainy day to avoid any protest after he gave a very unwelcome interview to VOA’s Peter Heinlein yesterday which angered most of us.
Our protest rally was not organized to unwelcome or welcome Hailemariam. It was a Freedom rally which was dubbed as May 18 the Freedom rally which forced the late Meles Zenawi to bow his head in front of his foreign supporters at Regan Building in DC on May 18 this year. The slogan we prepared were calling for all political prisoners to be released and the backers of the Ethiopian regime to stop financing dictatorship that violated civil rights of its citizens.
However, after the Sept. 27 interview that accuses the jailed activists and journalists as people who carry two hats oneHailemariam Desalegn led government in New York for legal activity and another for illegal activity we have no choice but to respond in kind and our rally soon turned denouncing Hailemariam as another Woyane from South. Hailemarim Desalegn is a living Meles Zenawi. Hailemariam is Woyane was shouted at the UN.
Some who wanted time to be given to Hailemariam started distancing themselves from Hailemariam after his VOA interview. New York has to “update” its slogan accordingly. Around 1pm fellow Ethiopians have arrived from DC area in Manhattan two hours earlier than the protest time. Taking advantage of the brake in the rain we started gathering around 1:30pm and start putting our placards and flags in the designated area. The police let us gather even before 3pm and we took advantage of that.
The on and off slight shower did not bother us for the first hour or so. In fact we were energized by the shower and slogans to denounce the dictatorship in Ethiopia went on continuously. Stop terrorizing the people of Ethiopia !!! Shame on you Obama for supporting dictatorship in Ethiopia. Shame on You USA for selecting Ethiopian dictators behind the scene. Ethiopians did not vote for Hailemariam. The slogan went on like that.
More people started coming around 3pm and the slogans went on both in English and Amharic. A Swedish media had an interview with us for less than half hour. The journalist asked the aim of our rally and what we thought of the recently released Swedish journalists from Ethiopian jail. We informed them that the Western media heard similar story years ago but ignored it and now forced to hear from their own people who suffered in Ethiopian jail. Nothing new for us or the people of Ethiopia who have been abused for the last twenty one years.
Other medias also covered our rally without asking for interview. The UN diplomats were educated on what is going in Ethiopia. Around 4:30pm the time Hailemariam addressed the UN 67th General Assembly there was similar address for the Ethiopian people from the plaza. The address challenged Hailemaram Desalegn to tell the whole truth about the injustice, corruption and human rights abuse in Ethiopia and to resign from his position or “Mideba” in Amharic as a messenger of Woyane/TPLF.
Unfortunately Hailemariam missed this historical opportunity and officially declared himself another Woyane/TPLF from South at UN. Some Woyane/TPLF supporters were tearing the flyers they were handed out of anger. In reply they were condemned by the protesters as “Hodeaderes”. The shower has completely stopped and the huge crowd passing around UN was educated on what is going in Ethiopia until 6pm.
Hailemariam Desalegn led government is identical to that of the late Meles Zenawi’s government. its backers are the same. Its vision is the same. Hailemariam himself without any apology declared that he is another Meles Zenawi. Hailemariam should get what ever Meles got in the last two decades whenever he travelled out of Ethiopia. New York has given him the first unwelcome and this will continue until Hailemariam is alive or forced to resign.