Sunday, October 7, 2012

ኢሀደግ ዴሞክራሲያዊ ተመሰረተ!!!


Ethiopian People's Revolutionary Democratic Front – Democratic (EPRDF D)
የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር - ዲሞክራቲክ   (ኢሕአዴግ ዲ)
Press Release - EPRDF Democratic
Addis Abeba
October 08, 2012
It is to be noted that Ethiopia has been in an economic and political growth in the
past two decades although there have been glitches here and there in every aspect
of our Nation.  Especially, since 2005  our great Country has been registering
double digit economic growth. These successes have been garnered through the
collaborative efforts of all four member parties, allies and the great people of
Ethiopia. Our  Front’s  oldest member, the Tigrean People’s Liberation Front
(TPLF) has spearheaded the struggle against the most dictatorial junta in Africa,
Mengestu Hailemariam’s Derg, which was finally overthrown through the
sacrifices of all EPRDF member parties and the Ethiopian people.
However, despite our hopes and convictions that power and leadership would be
evenly distributed and the TPLF will gradually decrease its hegemony, the
experience has been otherwise. We, the non TPLF member parties and allies of
EPRDF today, are under the full control of the TPLF and it arbitrarily meddles in
our internal workings. Our Party’s economic, security and political clout, as well as
our great Country (the current pandemonium within Oromo People’s Democratic
Organization (OPDP) is one example of this  interference).  This has  for long
created a huge political uncertainty and instability in the country. The international
community, the Ethiopian people and all concerned bodies have been worried that
this power monopoly could immediately change into civil war or an uncontrollable
state of affairs. Considering  these scenarios and  future risks, We, “Reform Seeking” members of EPRDF Executive Committee and Congress, have been
pushing and endeavoring for democratic reforms within our Front and Country.
We have been indefatigably arguing and calling the hardcore and extremist sect of
our Front’s leadership to make reforms  both  within our Front and Country. Our
group believes that for Ethiopia to continue a democratic and united country; our
Front should engage and  have  a  room for each and every Ethiopian party and
individual. Matters of the Front should be conducted in fairness and respect to all,
besides. We have lobbied that our Front’s policies and programs are obsolete and
ought to be reformed.
The hardcore and extremist sects of the EPRDF have so far paid deaf ear to our
requests and at times fired most of our colleagues labeling them “opposition
aficionados and neoliberlas”.   Similarly, our high hopes of immediate reforms
following the death of our great leader, the late Meles Zenawi, the incoming
leader, Hailemariam Dessalgn, sadly  reiterated the unwavering stands of the
hardcore and extremist groups of EPRDF.  He stepped on our repeated calls for
reforms and democratization within our Front and Country.
Therefore, we “Reform Seeking” members of the EPRDF,
- Convinced that  EPRDF members and  Ethiopians have the right and vested
interest to democracy, equality and freedom of/in their Country,
- Conscious that the continued  “unwillingness and refusal” of the  hardcore and
extremist sects of EPRDF endangers  the unity of our Front and the  national
security and regional stability of Ethiopia and the Horn of Africa,
- Aware that there is a necessity for an immediate and cross sectional reform in
policies, programs, leadership and structures of our Front, we “Reform Seeking”
members of the EPRDF declare that we have formed EPRDF Democratic (EPRDF
D).
We  therefore,  urge  the armed forces, member parties, regional states and
international community to stand with the new and reformed EPRDF D. In the
coming days, we will launch our website and publish our new leadership, Party
programs and policies.
08 October 2012
EPRDF Democratic CC:
EPRDF Secretariat
The Government of Ethiopia Communications Ministry
Office of the Prime Minister
African Union
United States of America State Department
International and local Media Organizations

ከፖለቲካ ፍጥጫው በስተጀርባ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)


ከኢየሩሳሌም አርአያ
በገዢው ሰፈር ጎራ ለይቶ ከተለኮሰው የቡድን ፖለቲካዊ ፍጥጫ እና ሴራ ጀርባ አገር እና ህዝብን የሚጎዳ አደገኛ ተግባር በግልጽ እና በስውር እየተካሄደ እንዳለ ከተለያዩPolitical cries inside Ethiopian ruling party የፓርቲው ምንጮች የተገኙ መረጃዎች ያመለክታሉ።
በተለይ በብአዴን እና በህወሃት ቱባ አመራሮች መካከል ስር ሰዶ የቆየው እና የአቶ መለስን ህልፈት ተከትሎ ያገረሸው የውስጥ ሽኩቻ ሁለት ቡድኖች የሃይል አሰላለፋቸውን ለማጠናከር «ይረዱናል » የሚሏቸውን የሌሎች ፓርቲ ሹማምንት እና የመከላከያ የጦር አዛዦች ከጎን የማሰለፉን ተግባር ቀጥለውበታል።ለግንዛቤ እንዲረዳ የሃይል አሰላለፉን በጥቂቱ በመዳሰስ ወደ ዋናው ነጥብ እናምራ።
ከበረከት እና ዓዜብ ጎን በመሰለፍ ቀዳሚ የሆኑት አቶ ተፈራ ዋልዋ እና አዲሱ ለገሰ ናቸው።አቶ አዲሱ በይፋ ከሚታወቀው የአየር መንገድ የቦርድ ሃላፊነታቸው ባሻገር ኮተቤ መስመር በሚገኘው እና «የአቢዮታዊ ዲሞክራሲ ማኔጅመንት ት/ቤት »ተብሎ በተከፈተው ተቋም ዋና ሃላፊ እና ለባለስልጣናት እንዲሁም ካድሬዎች መምህር ጭምር ናቸው። ከመለስ መታመም ወዲህ የህወሃት ካድሬ ላልሆኑ በአቶ አዲሱ እየተሰጠ ያለው ፖለቲካዊ ትምህርት ሳይሆን የበረከትን አቋም የሚያቀነቅን እና ህወሃትን የሚያጥላላ ቅስቀሳ ሆኖአል።
በሌላ በኩል ዓዜብ ከጎኗ ማሰለፍ የቻለችው ጄነራል ሰአረ መኮንን እና እንዲሁም በእርሳቸው የሚመራውን ጦር ነው ።በተጨማሪም ቴዎድሮስ ሃጎስ ይገኛሉ ።የዓዜብ አስገራሚ “አቋም” በሶፊያን አህመድም ላይ ተንጸባርቋል።”ለኤርትራ ካሳ “በሚል 2.1 ቢሊዮን ብር ለሻብያ በሚስጥር እንዲሰጥ በፊርማቸው ጭምር ከወሰኑት መካከል አቶ መለስ ዜናዊ፣ሙሉጌታ አለም ሰገድ ፣ሟቹ አቃቤ ህግ መስፍን እና ሶፊያን አህመድ ይገኙበታል።ዓዜብ ከዚህ በመነሳት “መለስን የማይክዱ ታማኝ “ካለቻቸው አንዱ ሶፊያን ናቸው ።
በተቃራኒው በነስብሃት በኩል ያለው የሃይል አሰላለፍ ለየት የሚያደርገው በነ በረከት ቂም የቋጠሩ “ተገፊ እና አድፋጭ”አመራሮችን እያቀፈ መቀጠሉ ነው ።ስዩም መስፍን ፣ሃይለኪሮስ ገሰሰ፣አባዲ ዘሞ ፣ቢተው በላይ . . . .. .በከፊል ይጠቀሳሉ ።
ስዩም ከስልጣን ተነስተው የቻይና አምባሳደር መሆናቸው ከተገለጸ በኋላ በውጭ ጉዳይ ቢሮ የተመደቡ ሰባት አባላት በሂልተን ሆቴል የምሳ ግብዣ አድርገውላቸው የነበረ ሲሆን በወቅቱም “ከስልጣን እንደምነሳ ምንም የማውቀው አልነበረም።አስቀድሜ ባውቅ ኖሮ ለእናንተም ብዙ ነገር አደርግ ነበር፤ አዝናለሁ። የበረከት ፣መለስ እና አዜብ ስራ ነው “ብለው ስዩም በቁጭት እንደነገሯቸው በስፍራው ከነበሩ ማወቅ ተችሏል። በሌላም በኩል ሃይለኪሮስ ለበረከት ከፍተኛ ቂም አላቸው ።ከቻይና ቀጥሎ የሱዳን አምባሳደር ተደርገው ነበር ።በኋላም በቃኝ ብለው ከፓርቲው በመውጣት የግል ንግድ ውስጥ ተሰማርተው ቆይተዋል ።አሁን ደግሞ ለበቀል ሲሉ የስብሃትን ቡድን ተቀላቅለዋል ።እንዲሁም በመለስ/በረከት የማይወደዱት እና ሃይለኪሮስን ተክተው በሱዳን አምባሳደር እንዲሆኑ የተመደቡት አባዲ ዘሞ ሌላው የፍልሚያው ተሳታፊ ናቸው ።ድፍረት የተሞላበት የተቃውሞ ሃሳብ በመሰንዘር እና መለስን ጭምር በመጋፈጥ የሚታወቁት ብቸኛው አባዲ ከዚህ በተጨማሪ በህወሃት ካሉ ባለስልጣናት ሙስና ውስጥ ካልገቡ ሁለት ሰዎች አንዱ ናቸው በማለት ምንጮች ይመሰክራሉ ።ሁለተኛው ደግሞ አባይ ወልዱ ናቸው ሲሉ ያክላሉ ። ከህወሃት የተባረሩት አምባሳደር አውአሎም ወልዱ ወንድም ናቸው አቶ አባይ ወልዱ ።ቢሆንም አባይ በጣም ደረቅ እና አምባገነናዊ ስብእናም እንዳላቸው ምንጮቹ አልሸሸጉም።
በዚሁ ወደ ዋናዎቹ ሁለት ርእሰ ጉዳዮች እናምራ፤ የበረከት እና ስብሃት ጎራዎች አንዱ የሆነው የልዩነት ፍጥጫ የአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ እና የአቶ ደመቀ መኮንን ሹመት ይገኝበታል። ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያምን በተመለከተ የተገኙ ተጨባጭ መረጃዎችን ለጊዜው እናቆያቸው ፤ትችት እና ወቀሳውንም እንዲሁ።ነገር ግን አቶ መለስ ማንኛውንም የፓርቲ አመራር ሲመለምሉ እና ሲያስመለምሉ የጀርባ ታሪኩን የሚያራምደውን አቋም . . . .መነሾ በማድረግ እንደሆነ የሚጠቁሙት ምንጮቹ አያይዘውም ፤ ተምሯል ፣ለሃገር እና ህዝብ ይሰራል. . .ወ.ዘ.ተ የሚለው በጭራሽ መስፈርት ሆኖ አይገባም ይላሉ ።የምልመላው ጥናት ቀንደኛ ተሳታፊ በረከት ሲሆኑ በመቀጠል የህወሃት አመራሮችም ይካፈላሉ ።ህወሃት ከበረሃ አንስቶ የተማረ አይወድም ፣ጠላቱ ነው ሲሉ የፓርቲው ምንጮች ያሰምሩበታል።
አቶ ሃይለማርያም ገና በጠዋት ለፓርቲው የተመለምሉበት የነመለስ-በረከት “መስፈርት”እንደተጠበቀ ሆኖ የመለመላቸው ተ/ማርቆስ ተ/ማርያም የተባለ እና አሁንም ድረስ ከጀርባ ሆኖ የደቡብ ክልል ባለስልጣናትን እንዲሁም መስተዳድሩን እያሽከረከረ ያለ ካድሬ ነው።ተ/ማርቆስ በደርግ ዘመን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ ምሩቅ የነበረ እና በአስተማሪነት የተመደበ ፣እንዲሁም ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተዛውሮ ሲሰራ ከቆየ በኋላ በ1982 አመተ ምህረት ገደማ የተባረረ ነው። ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ሲመጣ በአቶ ቢተው በላይ አማካይነት ተመለሰ ።ከዚያም በይፋ ያልተገለጸ ቁልፍ ስልጣን እንዲጨብጥ ተደረገ ፤በአጭሩ ሃይለማርያም ዛሬ ለደረሱበት የስልጣን ደረጃ ተ/ማርቆስ ለአቶ መለስ ያደረሰው የስለላ-ጥናት ውጤት ሲሆን ከዚሁ ጎን የባለቤታቸው ወ/ሮ ሮማን አቋም በነ መለስ “መስፈርት “ አሟልተው በመገኘታቸው ጭምር ነው ። በተመሳሳይ የበረከት ምልምል የሆኑት ደመቀ መኮንን በኢሰፓ አባልነት ይታማሉ ።
እነ ስብሃት ራሳቸው ሲከተሉት እና ሲያስፈጽሙት የነበረ በመሆኑ የሃ/ማርያም እና የደመቀ ሹመት በበረከት በኩል መከወኑ እጅግ አበሳጭቶአቸዋል።የጠቅላይ ሚንስትሩ ቀጣይ “አቋም” ይቀየራል ? ወይስ ከአሁኑ ማንጸባረቅ በጀመሩት የመለስ/በረከት አጥፊ መስመር ጉዞ ይቀጥላሉ ?የሚለው በተለያዩ ወገኖች ድብልቅልቅ ስሜት ፈጥሮአል ፡፤ለምሳሌ በቅርቡ በሰጡት መግለጫ ላይ “ቀይ መስመር፣ሰላማዊ እና ህጋዊ ባርኔጣ” በማለት ንጹሃን የህሊና እስረኛ ጋዜጠኞችን እና በሰላማዊ መንገድ የፖለቲካ እንቅስቃሴ በማድረጋቸው ብቻ ለእስር የተዳረጉ ወገኖችን ያለ ሃፍረት በጅምላ ወንጅለዋል።በዚህ ሳያበቁ “ከሻብያ ጋር በጠረጴዛ ዙሪያ መነጋገር እንፈልጋለን “ሲሉ የመለስ ፣በረከት እና ስብሃት… አቋም ቃል በቃል አንጸባርቀዋል።በረከት፣መለስን የተኩት የህወሃት ሊቀመንበር አባይ ወልዱ “ከተቃዋሚዎች ጋር ድርድር የማይታሰብ ነው “እያሉ በጥላቻ የታጠረ አቋማቸውን ሲገፉበት በሚስተዋልበት ተጨባጭ ሁኔታ ዛሬም ሻእቢያ እግር ስር በመደፋት ልምምጥ እና ልመናው መቀጠሉ ፣በአንጻሩ በአገር ውስጥ እና በውጭ ያሉ የተቃዋሚ ሃይሎች የድርድር ጥያቄ መገፋቱ እና አፈናው ተጠናክሮ መቀጠሉ ሲታይ ፦በእርግጥም ከሃ/ማርያም ጀርባ ያለው “ሹፌር”ለኢትዮጵያ እና ህዝቧ ጥቅም ምንም ግድ የሌለው እንደሆነ በቀላሉ ያሳያል ይላሉ እነዚሁ ወገኖች ።
ወደተከታዩ ነጥብ ስንሻገር በአስደንጋጭ ሁኔታ በሃገሪቱ ተጠናክሮ የቀጠለውን የሙስና ዘመቻ እናገኛለን ። በግልጽ እና በስፋት የሙስናውን መንደር ከተቀላቀሉት እና “ተከታይዋ ወይም ግልገሏ አዜብ”የሚል ቅጽል የወጣላቸው የበረከት ስምኦን ባለቤት አሰፉ በቀዳሚነት ትጠቀሳለች ።በረከት “አሲ”እያሉ በቁልምጫ የሚጠሯት አሰፉን ጨምሮ 6 የቤተሰብ አባላት በፓርቲው አባላት “ደቂ ማዘር” በሚል መጠሪያ ይታወቃሉ ።የታምራት ላይኔ ባለቤት የዚሁ ቤተሰብ አባል ስትሆን ከብአዴን የወጣችው (ከ6ቱ)እሷ ብቻ ናት ።የታደሰ ጥንቅሹ ባለቤት እንዲሁ የአሰፉ ቤተሰብ አካል ናት ።
የበረከት ባለቤት አሰፉ የመንግስት ስራ በመተው ወደ ከፍተኛ ንግድ መግባቷ ምንጮቹ አረጋግጠዋል። በአስመጭና ላኪ ንግድ የተሰማራችው አሰፉ በተለይ ወደ ዱባይ እና ሳኡዲ የተዘጋጁ የከብት ስጋ እና ቡና በመላክ እንዲሁም ከዱባይ እና ቻይና የሞባይል ቀፎዎችን የመኪና መለዋወጫ እቃዎችን እና የተለያየ ይዘት ያላቸውን ጄነረተሮች በማስመጣት ንግዷን አጧጡፋለች ።አብዛኞቹ ቀረጥ ሳይከፈልባቸው በጉምሩክ ሰትት ብለው እንደሚያልፉ ሲታወቅ የአዜብ ቀጥተኛ ድጋፍ እና ትእዛዝ እንዳለበት ተጠቁሞአል። አብዛኛውን ጊዜ ሁለቱም አብረው እንደሚያሳልፉ ምንጮቹ ገልጸዋል። በአስር ሚሊዮኖች የሚገመት ዶላር በመዛቅ ላይ የምትገኘው የበረከት ሚስት አሰፉ ለህወሃት ስር የሰደደ ጥላቻ እንዳላት የገለጹት እነዚህ ወገኖች በተደጋጋሚ ይህን አቋሟን በይፋ ስታንጸባርቅ መታየቷን አስታውቀዋል።
በሌላም በኩል አባይ ፀሃዬ ለበርካታ ባለሃብቶች በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ብድር በመፍቀድ በቅርብ ስጋ ዘመዶቻቸው በኩል ሃብት እንዳካበቱ ታውቆአል ። ቀደም ሲል የነበራቸውን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቦርድ ሃላፊነት ተገን አድርገው የፈጸሙት ዘረፋ ነው።የሙስናው ተዋናዮች አምስት የአባይ ጸሃይዬ የቅርብ ዘመዶች ናቸው ። ባለሃብቶችን በማግባባት ደላላ ሆነው እየቀረቡ በተፈለገው መጠን የገንዘብ ብድር ማሰጠት እንደሚችሉ ከገለጹ በኋላ ያለምንም ውጣ ውረድ አባይ ጸሃዬ እንዲፈቅዱ ይደረጋል። ከብድሩ እስከ 50 ሚሊዮን ኮሚሽን ይወስዱ እንደነበር ተጠቁሞአል ።ተመሳሳይ ተግባር አቶ ግርማ ብሩ ይፈጽሙ እንደነበር ምንጮቹ አያይዘው ገልጸዋል። በተለይ “ራዲሰን”የተባለው እና ካዛንችስ አካባቢ የተገነባው ባለአምስት ኮከብ ሆቴል ለግንባታ ተብሎ የተፈቀደለት 400 ሚሊዮን የብድር ገንዘብ እንደሆነ ሲረጋገጥ ከዚህ ገንዘብ ባለስልጣናቱ በኮሚሽን መልክ 150 ሚሊዮን ኪሳቸው እንደከተቱ ተረጋግጦአል። በጣም የሚገርመው ሸራተን ሆቴል እንኳን በአንድ መቶ ሰባ ሚሊዮን እንደ ተገነባ በይፋ እየተነገረ ለዚህኛው ሆቴል ግን ሁለት እጥፍ በብድር ስም ተፈቅዶ ሲመዘበር አቶ መለስ ጭምር ያውቁ ነበር ።በማያያዝም በባንክ ብድር የተሰራው ሸራተን ላለፉት 15 አመታት ብድሩን ያለመክፈሉና ባለፈው አመት ባንኩ የመሰረተው ክስ እንዲቆም መደረጉ አስገራሚ ሆኖአል ።ይህ እዳ ሳይከፈል በባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አቶ በረከት ስምኦን ትእዛዝ 942 ሚሊዮን ብር ለሼሁ ድርጅቶች መፈቀዱ እና በቅርቡ ደግሞ ታግዶአል መባሉ እንቆቅልሽ ከመሆኑም ባሻገር ምን ያክል የተበላሸ እና ከቁጥጥር ውጭ የሆነ ስርአት አልበኝነት በሃገሪቱ መንገሱ አመላካች ነው ተብሎአል ።በነገራችን ላይ አቶ በረከት ወደ ደቡብ አፍሪካ በሼሁ ቻርተር አውሮፕላኖች እንደሚመላለሱ ምንጮቹ አረጋግጠዋል።
በሌላም በኩል በቃሊቲ- አቃቂ በ7 ቢሊዮን የተቋቋመው ግዙፍ የብረት ማቅለጫ ፋብሪካ ሲጠቀስ ከጀርባ የአንበሳው ድርሻ ባለቤቶች ስዩም መስፍን እና አዲሱ ለገሰ ይገኛሉ ። ከዚህ በማስከተል በተለያዩ ባለስልጣናት የተገነቡ እና እየተገነቡ ያሉ የሙስና ውጤቶች እንመልክት ።በትግራይ መቀሌ ከተማ “ለአካባቢ የአየር ጥበቃ “በሚል ተተክሎ የነበረውን ደን በመጨፍጨፍ መሬቱን የተቀራመቱት ስብሃት ነጋ ፣ቴዎድሮስ ሃጎስ ፣ሃለቃ ጸጋይ፣ጎበዛይ ፣ኪሮስ ቢተው፣ተክለወይኒ፣… ዋና ዋናዎቹ ናቸው ።”አፓርታይድ መንደር”በሚል በነዋሪው በተሰየመው በዚህ ቦታ የተደረገው የአደባባይ የመሬት ቅርምት የተቃወመ የማዘጋጃቤት ሃላፊ ከስልጣን ተነስቶ እስካሁን የደረሰበትም አይታወቅም ።የተጠቀሱት የህወሃት ሹማምንት እጅግ ምርጥ እና ዘመናዊ ቪላ በጥድፊያ እያስገነቡ እንዳሉ ሲታወቅ ባለ ሁለት እና ሶስት ፎቅ የሆኑት ቪላዎች ከአስር ሚሊዮን ብር በላይ ለእያንዳንዱ ቤት ግንባታ መድበው ስራውን ወደ ማጠናቀቅ መድረሳቸውን ማረጋገጥ ተችሎአል ። በስምንት ሚሊዮን ብር የተገነባው የኪሮስ ቢተው ዘመናዊ ባለ ሁለት ቪላ ግንባታው በቅርቡ እንደተጠናቀቀ ታውቆአል።
ሽማግሌው ስብሃት በቀድሞው የአየር ሃይል ም/አዛዥ ጄነራል ሰለሞን እና በአሜሪካ በሲያትል እና በዋሽንግተን ዲሲ በሚኖሩ ስምንት የስብሃት የአጎት እና የአክስት ልጆች ስም በአክሲዮን ሽፋን የከፈቱት “ሉሲ አካዳሚ”ከሙስና የተገኘ ትልቅ የገቢ “ዘረፋ” ምንጭ ሆኖአል ።አካዳሚው በገርጂ እና ሳር ቤት – ባለ ስድስት ፎቅ ህንጻ አቅፎአል። የፌደራል ፖሊስ ም/ኮሚሽነር ሃሰን ሺፋ በቦሌ ያስገነቡት ባለሁለት ቤት ቪላ ተጠናቆ በየወሩ 25 ሺህ ብር መከራየት ጀምሮአል። የጄነራል ሳሞራ ቪላ ከለንደን ካፌ ፊት ለፊት ሲገኝ ከ1997 አመተ ምህረት ጀምሮ በየወሩ 30 ሺህ ብር ይከራያል። ባለ ሶስት ፎቅ የአባዱላ ቪላ ከሳሞራ ቪላ ቀጥሎ ሲገኝ ከሚያዚያ 97 አመተ ምህረት ጀምሮ በየወሩ 4 ሺህ ዶላር ለነጮች ይከራያል። ቦሌ ኤርፖርት መግቢያ ከኖክ ማደያ ጀርባ የብርሃነ ገ/ክርስቶስ እና የአዲስአለም ባሌማ ተወዳዳሪ ያልተገኘለት ባለሶስት ፎቅ ምርጥ ቪላዎች ይገኛሉ።በ1988 አመተ ምህረት የተገነቡት የሁለቱ ቪላ ሁለት የአሜሪካ ከፍተኛ መኮንኖች እያንዳንዳቸው በአራት አራት ሺህ ዶልር ተከራይተውታል። ከኢምፔሪያል ሆቴል አጠገብ የተገነባው እና በሰባት ሚሊዮን ብር ወጪ የተሰራው የተፈራ ዋልዋ ባለ ሦስት ፎቅ ቪላ በወር 30 ሺህ ብር መከራየት የጀመረው በ97 አመተ ምህረት መጨረሻ ነበር።የሙስናው ዝርዝር እና ስፋት በጣም ሰፊ ነው ።ወደ ውጭ እየሸሸ የሚገኘው የሃገር እና ህዝብ ሃብት ሳይካተት ማለት ነው ።
በዚህ አጋጣሚ ሳይጠቀስ የማይታለፈው በታይላንድ ባንኮክ የሚጸመው አሳዛኝ የሙስና ድራማ ነው። በርካታ የህወሃት ጄነራሎች እና ሌሎች ባለስልጣናት ከራሳቸው አልፈው የቅርብ ዘመዶቻቸውን እና ውሽሞቻቸውን ጭምር በከፍተኛ ወጭ ማሳከምን ተያይዘውታል። ከህወሃት ጀነራሎች መካከል ጄነራል ሰአረ እና ጀነራል ተስፋዬ በዋናነት ይጠቀሳሉ ።የሆስፒታሉ የህክምና ወጭ እንዲሁም የሚያርፉባቸው ባለ5 ኮከብ ሆቴሎች (ኢንተር ኮንቲኔታል እና ቻል ዲፖሎ )ናቸው ። በየሶስት ወሩ በሚቀርበው የክፍያ ዝርዝር ሪፖርት ከሰባት እስከ አንድ ሚሊዮን ዶላር እንደሚከፈል የቅርብ እማኞች ያስረዳሉ።
ከፍተኛ ክፍያ የተፈጸመው ለአባዱላ ገመዳ ልጅ ነው ።የሶስት አመቷ ህጻን ዲቦራ አባዱላ ስትወለድ የአንጀት ፣የሳምባ እና የአእምሮ ችግር ነበረባት ።ለሁለት አመት ተከታታይ ህክምና ተደረገላት ።የአባዱላ ባለቤት ራሄል ልጇን ያን ያክል ጊዜ ስታስታምም ባለአምስት ኮከብ ሆቴል ቪላ ተከራይታ ነበር ።የሁለት አመት የተከፈለው አጠቃላይ ወጪ 2.5 ሚሊዮን ዶላር እንደነበር ተረጋግጦአል። በአሁኑ ወቅት አባዱላ ሼሁን ተገን አድርገው ከበረከት ጎን ተሰልፈዋል።
በመጨረሻም አዜብ መስፍንን ከኤፈርት ለማስነሳት ሰፊ ዘመቻ በህወሃት አመራር ውስጥ መከፈቱን ለማወቅ ተችሎአል። የፓርቲው ሰዎች “የአዜብ ጸሃይ እየጠለቀች ነው “ብለዋል ።በቅርቡ አሜሪካ የቀሩት የአዜብ ምክትል ጌታቸው በላይ ለሽማግሌው ስብሃት ነጋ የቅርብ ዘመድ ሲሆኑ ከአቶ መለስ ጋር ደግሞ አብሮ አደግ ጎረቤቶች እንደነበሩ ታውቆአል። በኤፈርት የአዜብ ፈላጭ ቆራጭነት ያስመርራቸው እንደነበር ሲታወቅ ከነበራቸው የሚንስትርነት ስልጣን ወደታች መንሸራተታቸው ቅሬታ አሳድሮባቸው እንደቆየ የቅርብ ምንጮች ጠቁመዋል ። የሙስናው ጉዳይ እንዲጣራ አንድ ፖለቲከኛ ጥቆማ ስጥተዋል።

ኦህዴድ በ“መደብ ትግል” መተላለቅ ጀመረ!


ኦህዴድ በ“መደብ ትግል” መተላለቅ ጀመረ!


ጎልጉል

junedin abadula kuma
በኦህዴድና በህወሓት መካከል የነገሰው ልዩነት ይፋ የወጣው ዛሬ አይደለም። አርሲ ላይ ማዕከል አድርጎ የተደራጀውን የጁነዲንን ኦህዴድ አባዱላ ሙሉ በሙሉ ከናዱት በኋላ ከፈጣጠሩ ጀምሮ ሰንካ ያልተለየው ራሱ ኦህዴድ ውስጥ ውስጡን ሁለት ቦታ ተገምሶ ቆይቷል።
በዘመነ “ህንፍሽፍሽ” ህወሓት ለሁለት በተሰነጠቀበት ወቅት “በህወሓት የውስጥ ጉዳይ ውስጥ ጣልቃ በመግባት መግለጫ አናወጣም” በማለታቸው ከድርጅትና ከሃላፊነታቸው ተባርረው በነበሩት ኩማ ደመቅሳ ጠቋሚነት ጨፌ ኦሮሚያ አዳራሽ የኦሮሚያ ፕሬዚዳንት ሆነው በ1997 ዓም የተመረጡት አባዱላ ገመዳ ሥልጣን በያዙ ማግስት የጁነዲንን “አርሲ ተኮር” ካቢኔ ሲንዱት ጁነዲንና ደጋፊዎቻቸው ደስተኛ እንዳልነበሩ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ይናገራሉ።ጁነዲን ስልጣን ባስረከቡ በደቂዎች ውስጥ ከጋዜጠኛ ቀርቦላቸው ለነበረ ጥያቄ “ከስልጣን እንደምወርድ ከሁለት ዓመት በፊት አውቀው ነበር” ብለው መመለሳቸውን በስፍራው የነበሩ ያስታውሳሉ።
በዚሁ ሳቢያ በተፈጠረ መቧደን የነጁነዲን ቡድን አባዱላን ለማሰመታት የተደራጀው በጊዜ ነበር። አባዱላን ለማስወገድ ይቻል ዘንድ ተባራሪው ፕሬዚዳንት ጁነዲን የአባዱላ ምክትል የነበሩትን ሙክታር ከድርን ደጋፊያቸው አደረጉ። ይህ መቧደን በተጋጋለበት ወቅት አባዱላ ከሼኽ መሃመድ አላሙዲ ጋር ከፍተኛ ጸብ ውስጥ ገብተው ነበር። አባዱላ ለበታች አመራሮች አላሙዲ አስፈላጊውን ግብር እንዲከፍሉ፣ ያላለሙትን መሬት እንዲነጠቁና የመሳሰሉትን ርምጃዎች በካቢኔ በማስወሰን ተግባራዊ ያደረጉበት ያ ወቅት አባዱላ በኦሮሚያ ተወዳጅነት ያተረፉበት፣ በተዛማጅ ደግሞ ወንበራቸው መንገዳገድ የጀመረበት ወቅት ስለመሆኑ ሽኩቻውን የሚከታተሉ በስፋት የሚያወሱት ጉዳይ ነው።
የውጥኑ መነሻና መድረሻው የደረሳቸው አባዱላ በኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ግምገማ የሙስና ጉዳይ ከመነሳቱ በፊት  አስቀድመው ሃጢያታቸውን ተናዘዙ። “ይህንን ቤት ይዤ ለመታገል አይመቸኝም” በማለት ጥይት እንዳይበሳው አድርገው ወዳጆቻቸውና “ተጠቃሚዎች” የገነቡላቸውን ዘመናዊ መኖሪያ ቤት ካርታና የባንክ እዳ ለድርጅቱ አበረከቱ። ሌሎቹም ያላቸውን እንዲያስረክቡ ሲጠየቁ ጁነዲን አዳማ ያላቸውን አንድ ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ እሰጣለሁ አሉ። አዲስ አበባና ለገጣፎ ስላላቸው ህንጻ ዝምታ መምረጣቸውም ይፋ ሆነ። እነ ሽፈራው ጃርሶ፣ ግርማ ብሩ ግን የመንግስት ቤት ውስጥ እየኖሩ በዶላር የሚያከራዩትን ቤት ለማስረከብ ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ።

ሙክታር ከድር
በወቅቱ የመለስ ድጋፍ የነበራቸው አባዱላ በግምገማው መጨረሻ እነ ሙክታርን ረቱና ከኦሮሚያ አባረሩ። አካባቢያቸውንም አጸዱ።
አባዱላን ለመምታት የሚደረገው ፍትጊያ ቢያይልም አዲሱ ካቢኔ አባዱላን “ጃርሳው” በማለት ተቀበለ። በጉባኤና በግምገማ “አባዱላን የሚነካ ወዮለት” ማለት ጀመረ። አባዱላም “ልማትን አፋጥኑ እንጂ የፈለጋችሁን አላማና አመለካከት መያዝ ትችላላችሁ። እኔ ሃላፊነቱን እወስዳለሁ” በማለት በወጣቶች የገነቡትን ካቢኔ ስሜቱን አጋሙት። በዚህ መካከል 2002 ምርጫ ሲመጣ በድንገት አባዱላ ኦሮሚያ ክልል እንደማይወዳደሩ ከላይ መወሰኑ ተሰማ። ካድሬው፣ ምክርቤቱና ካቢኔው ውሳኔውን “አንቀበልም” አለ።

ብርሃኑ አዴሎ
በቆረጣ ባለሃብቱ (አላሙዲ) ላይ ተንጠላጥሎ በሙስና መሽተቱና የባለሃብቱ ታዛዥ እንደሆነ የሚነገርለት ብርሃኑ አዴሎ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ሃላፊነት ሲወገድ ሙክታር ከድር ተክተው ተሾሙ። ሹመቱ የባለሃብቱ እጅ እንዳለበት አብነት ገ/መስቀል ሸራተን አዲስ ስም እየጠራ ወሬውን የአልኮል ቁርስ በማድረግ አስቀድሞ ሲናገር የሰሙ ይመሰክራሉ። በድርጅት ከኢህአዴግ ጋር፣ በጽህፈት ቤት ከጠ/ሚኒስትሩ ጋር የቀረቡት ሙክታር ከድር አባዱላ ገመዳን ለመጎሸም አጋጣሚው ተመቻቸላቸው።

አብነት ገ/መስቀል
በዚህ መሃል አባዱላ በድጋሚ ክልሉን እንዲመሩ በኢህአዴግ ምክር ቤት የተወሰነውን ውሳኔ የኦህዴድ ስራ አስፈጻሚ ከጁነዲን፣ ከሙክታር፣ ከሱፊያንና ከሽፈራው ጃርሶ በስተቀር የተቀሩት ተቃወሙ። ምክር ቤቱም አወገዘው። የበታች አመራር ማብራሪያ ጠየቀ። በዚሁ ሳቢያ በረከት ስምኦን አዳማ ወረዱና የኦህዴድን ጠቅላላ ጉባኤ ሰበሰቡ። ካድሬው ሳይፈራ በረከትን ሞገተ። በረከት የድርጅት ውሳኔ መከበር እንዳለበት በማስፈራራት ተናገሩ። ካድሬው አሻፈረኝ አለ። አባዱላ “እባካችሁ” በማለት ተማጸኑ። በሁለት ስብሰባዎች አልበገርም ያለው የካድሬው ተቃውሞ በሶስተኛ ስብሰባ አባዱላ ተማጽኖ አቅርበው፣ ካድሬው አልቅሶና ፈርቶ አባዱላን ለመሸኘት ተስማማ። በረከት ስምዖንና ህወሓት ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ቂም እንደያዙ ስለቆዩ ኦህዴድን ለማጥራት አሁን አጋጣሚው እንደተመቻቸላቸው አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ፡፡
አሁን በኦህዴድ ውስጥ ተፈጠረ የተባለው ቡድን ሲወርድና ሲንከባለል ቆይቶ መለስን በሚተካው አመራር ማንነት ላይ የድርጅቱ ምክር ቤትና ካድሬ ተቃውሞውን በግልጽ አወጣው። ህወሓቶችም በዚህ መልኩ መቀጠል የማይችሉበት ደረጃ ደረሱ። ሁለት ተጻራሪ ቡድኖች የሚያካሂዱት አይነት የመደብ ትግል እየተደረገ መሆኑ ይፋ ሆነ። ለህወሓት ትዕዛዝ እንደቀድሞው መታዘዝ ያቆመው ኦህዴድ ይህንን አቋም ከየት አመጣው?
አዲሱ ኦህዴድ
ቀደም ሲል ከነበረው ኦህዴድ ይልቅ አባዱላ ያደራጁት ኦህዴድ በወጣቶች የተገነባ፣ በካቢኔ ደረጃ አንደኛና ሁለተኛ ዲግሪ ያላቸውና ቀደም ሲል በኦነግ አስተምሮ የበቁ እንደሆኑ ይነገራል። ስለድርጅቱ በቅርበት የሚያውቁ እንደሚሉት አዲሱ ኦህዴድ በማክረር ፖለቲካ የተለከፈ አይደለም። ነገር ግን ኦሮሞ አገሪቱን መምራት አለበት የሚል፣ የመለስ ሂሳብ ባስቀመጠው ስሌት መሰረት ጠ/ሚኒስትርነቱን ያለማቅማማት መረከብ አለብን የሚል አቋም ያራምዳሉ።
አሮጌው ኦህዴድ ኦነግን መታገል ባለመቻሉ አዲሱ ኦህዴድ የኦነግና  የኦሮሞ ብሄራዊ ኮንግረንስ የወጣት ክንፍ አባል የነበሩትን በማስኮብለል አባል ማድረጉ ድርጅቱን እንደበረዘው ጭምጭምታ ይሰማ ነበር። እነ ጁነዲን ድርጅቱን ልቅ በማድረግ ለዚህ አደጋ የዳረጉት አባዱላ እንደሆኑ በተደጋጋሚ ቢያቀርቡም አባዱላ ለህወሓት ባለስልጣኖች፣ ለአዜብ፣ ለመለስ ጠባቂዎች፣ ለደህንነት ሰዎችና አስፈላጊ ናቸው ለሚባሉት ሁሉ የክልሉን መሬት በንግድ ስምና በመኖሪያ ቤት ስም በማደል ስለተወዳጁ፣ በሌላ አነጋገር ስላነካኳቸው ክሱ ተቀባይነት ሳያገኝ ቆየ።
አዲሱ ኦህዴድና አመራሮቹ ሁሉንም አካሄድ ስለሚያውቁና የአባዱላ ውሳኔ አስፈጻሚዎች በመሆናቸው ሌሎች በመሬት ንግድ ገንዘብ ሲያፍሱ “እኛስ” በማለት በጋራ ገንዘብ ወደ ማምረቱ አተኮሩ። የሚፈሩ የነበሩ የህወሓት ባለስልጣናት መሬት ፍለጋ በየማዘጋጃ ቤቱ ደጅ ሲጋፉ መናናቅ ተፈጠረ። ህወሓት ገንዘብ ሲያሳድድ ቀደም ሲል የነበረውን ስም አጣ። ኦህዴዶች በስም እየጠሩ ለህወሓቶች ምጽዋት እንደሚሰጡዋቸው ይናገሩ ጀመር። ቀደም ሲል ከነበረው ፖለቲካ እምነት ጋር ተዳምሮ ህወሓት ተናቀ፤ ተጠላ – በተለይም በኦህዴድ። ኦህዴድ የአመራሩ ባለቤት መሆን እንዳለበት ካድሬው በግልጽ ያወራ ጀመር። በዚሁ ሳቢያ በርካታ አዳዲስ የካቢኔ አባላት በሙስና ስም እንዲታሰሩ ተደረገ። ኩማ ደመቅሳ ቡራዩ በተካሄደ ዝግ ስብሰባ ተልዕኳቸውን አሳኩ። አዲሱ ኦህዴድ አጥብቆ የሚጠላቸው ኩማ መጨረሻቸው ባይታወቅም ከፊት መስመር ሆነው የማስተናበሩን ስራ እየመሩ ነው። አዲሱ ኦህዴድ ከሞላ ጎደል ይህ ነው። በሙስና የሸተተ፣ በአመላካከት የተሻለ፣ ዥንጉርጉር አቋም ያካተተ፡፡
“በአንድ ድርጅት ውስጥ የመደብ ትግል ካለ መተላለቅ ተጀምሯል ማለት ነው”
ኦህዴድ እንደ ድርጅት ሊቀጥል የማይችልበት ደረጃ መድረሱን የሚያመለክቱ መረጃዎች እየወጡ ነው። በአንድ ፓርቲ ውስጥ “የመደብ ትግል” የተባለ ግምገማ መካሄዱን ተከትሎ ከህወሓት መሰንጠቅ ቀጥሎ በኢህአዴግ ታሪክ ትልቅ የተባለ የማጥራት እርምጃ ይወሰዳል ተብሎ ተገምቷል። ጉዳዩን አስመለክቶ ያነጋገርናቸው “የመደብ ትግል ካለ መተላለቅ ተጀምሯል ማለት ነው” ብለዋል።
በልዩ ጥበቃ ካለፈው እሁድ ጀምሮ ለአራት ቀናት በተካሄደው የኦህዴድ ምክር ቤት ግምገማ ድርጅቱ እንደ ድርጅት መቀጠል የማይችልበት ደረጃ መድረሱና፣ ለድርጅቱ የተቀመጠው መስመር መጣሱ በዋናነት የተነሱ የግምገማው መነሻ ጉዳዮች መሆናቸውን የጎልጉል ምንጮች ገልጸዋል።
በየሳምንቱ ረቡዕ የሚታተመው ሰንደቅ የተባለው ጋዜጣ “ የሰላ መደባዊ ትግል” መካሄዱን አስነብቧል። በረከት ስምዖን ከኋላ ሆነው የሚመሩት ሰንደቅ ጋዜጣ “ስርዓቱን ለማኖር ሲባል የድርጅቱን መስመር በርዘው በሚንቀሳቀሱት አመራሮች ላይ የማያዳግም እርምጃ የሚወሰድበት ትግል” ሲል ባልተለመዱ የግምገማ ቃሎች ኦህዴድ ውስጥ የተከሰተውን ችግር ይፋ ያደረገው ዜና ችግሩን ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ሹመት ጋር አያይዞታል።
ጎልጉል የአዲስ አበባ ምንጮች እንደሚሉት ግን ኦህዴድ የጠቅላይ ሚኒስትርነት መቀመጫው እንዲሰጠው አለመጠየቁ ካድሬዎቹን አበሳጭቷል። በበታች አመራሮች አማካይነት የተነሳውን የቆየ ጥያቄ የድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ በኢህአዴግ ምክር ቤት ስብሰባ ወቅት ያቀርባል ተብሎ ሲጠበቅ አለማቅረቡ አሁን ይፋ ለወጣው “የመደብ” ችግር ዋና መንስዔ ነው።
በኦህዴድ ምክር ቤት ደረጃ አቋም የተያዘበትን ጉዳይ ወደ ጎን በመተው ለሃይለማርያምና ለደመቀ ድምጽ በመስጠት የተመለሰው ሥራ አስፈጻሚ የልዩነት አቋም አራምደዋል በተባሉት በምክርቤቱ አባላት፣ በበታች አመራርና ካድሬዎች ዘንድ ቅሬታ አስነስቷል። በዚሁ ሳቢያ የቆየው ክፍፍልና ቁርሾ ይፋ ሊወጣ ችሏል።
ከሥራ አስፈጻሚው ጀምሮ በተዋረድ ባለው መዋቅር እስከ ቀበሌ የደረሰው የልዩነት ደረጃ በመካረሩ “የመደብ ትግል” የሚል ስያሜ የተሰጠው ግምገማ እንዲካሄድ ምክንያት ሆኗል። ጎልጉል ያነጋገራቸው የፖለቲካ ተንታኝ “በአንድ መስመር ላይ ሆነው በሚሰሩ የአንድ ድርጅት አባላት መካከል የመደብ ልዩነት ሊከሰት አይችልም። ከተከሰተም ልዩነቱ እስከመጫራረስ የሚያደርስ ይሆናል” ሲሉ የግምገማው ውጤት መዘዝ ሊያስከትል እንደሚችል ያስረዳሉ።
“የመደብ ትግል” አሉ አስተያየት ሰጪው “የመደብ ትግል ከሁለት በላይ በሆኑ ተጻራሪ ሃይሎች መካከል የሚካሄድ አሸናፊና ተሸናፊ ያለው ትግል ነው። ኦህዴድ ውስጥ በትክክል የመደብ ትግል የሚባል ግምገማ ከተነሳ ጉዳዩ አሳሳቢ ነው። የመደብ ትግል ብሎ ግምገማ ስለሌለ ድርጅቱ ከፍተኛ አደጋና የህልውና ቀውስ ይገኛል ማለት ነው። ኦህዴድ በመደብ ልዩነት ችግር ከተመታ ፓርቲው እንደ ፓርቲ መቀጠል አይችልም ማለት ነው። ቀውሱ ወደ ሌሎቹም ድርጅቶች የመዛመት ዕድሉ በጣም ከፍተኛ ይሆናል” በማለት አስተያየታቸው ሰጥተዋል።
መለስ የቆፈሩዋቸው ጉድጓዶች በሚል ርዕስ ስማቸው ለጊዜው እንዳይጠቀስ ጠይቀው ከጎልጉል ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት የኢህአዴግ ሰው ከወር በፊት“የወንበር ጥያቄው መነሳቱ አይቀርም። ካድሬውና የበታች አመራሩ ድሮም ጀምሮ ሃሳቡ አለው። ግምገማ እየተባለ በሰርጎ ገቦች እየተሰለሉ እየተወገዱ እንጂ እስከዛሬም አይቆይም ነበር። ያም ሆነ ይህ መለስ ስለሌሉ የወንበር ቡቅሻው የማይቀር ነው። በየድርጅቱ አመራሮች ዘንድ የሌባና ፖሊስ፣ የሃይል ሚዛንና ቅኝት፣ አሰላለፍን የማሳመር ሰልፍ እየታየ ነው። አሁን በዝርዝር የማልናገረው አንዳንድ የመናድ ምልክቶችም አሉ”  በማለት ቅድመ ትንበያቸውን አስቀምጠው ነበር። (የቃለምልልሱን ሙሉ ቃል ለማንበብ እዚህ ይጫኑ)
የግምገማውን ውጤት አስመልክቶ በማስጠንቀቂያ የሚታለፉ፣ በህግ የሚጠየቁ፣ የፖለቲካ ውሳኔ የሚተላለፍባቸው እንደሚኖሩ ይጠበቃል። የበረከት ጋዜጣ ሰንደቅ እንዳለው መሸፋፈንና ማድበስበስ የለውም በተባለለት “እርቅ የሌለው ትግል” ሲጠናቀቅያለመከሰስ መብታቸው ተነስቶ ለህግ የሚቀርቡ አሉ። የጎልጉል የመረጃ ምንጮች እንደሚሉት የኦህዴድ ሰዎች በፓርላማና በድርጅት ለመለስ እያጨበጨቡ፣ እያንቀላፉ ባጸደቁት ህግ መቀጣታቸው አይቀሬ ነው።
ከፖለቲካው በተጨማሪ ከሃይማኖት ጋር በተያያዘ “አሸባሪነትን ለሚቀሰቅሱና አገሪቱ በሸሪዓ ህግ እንድትመራ ለመጠየቅ እቅድ ከያዙ ክፍሎች ጋር በማበርና ዓላማቸውን ተግባራዊ እንዲያደርጉ ውስጥ ውስጡን የማሳለጥ ስራ ሲያከናውኑ ነበሩ” የተባሉም አሉ። ምንጮቻችን እንዳሉት ኢህአዴግ የሙስና ፋይል የሚከፍትባቸውም አይታጡም።
ህወሓቶች የሚመሩት የስለላው ሃይል አባላቱ ለሚከሰሱበት ክስ ሰነድ አዘጋጅቶ እንደጨረሰ ያስታወቁት ክፍሎች ከኦህዴድ አመራሮች መካከል ቀደም ሲል በጁነዲን ሳዶ፣ አባዱላ ገመዳና አሁን ደግሞ ኩማ ደመቅሳ መካከል ያለውን አሰላለፍና ልዩነት ሲከታተል ነበር። በዚሁ መሰራት ስም ባይዘረዝሩም እርቅ የሌለበት ግምገማ ሲጠናቀቅ ቀደም ሲል ጀምሮ የነበሩ ጉዳዮች እንደ አዲስ እንደሚነሱ የጎልጉል ምንጮች አስታውቀዋል።
(ለጽሁፍና ለትረካ ይመች ዘንድ አቶ ከማለት ለተቆጠብንበት ሁሉ ይቅርታ እንጠይቃለን)