Thursday, May 2, 2013

የታላቁ ሰማእት የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ተነሳ


የታላቁ ሰማእት የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ተነሳ

ሚያዚያ ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ከአዲስአበባ የቀላል ባቡር ዝርጋታ ጋር በተያያዘ ይነሳል በመባሉ ከፍተኛ ተቃውሞ አስነስቶ የነበረው የአቡነ
ጴጥሮስ ሐውልት ዛሬ ለዓመታት ከቆመበት የክብር ቦታ ተነሳ፡፡
መንግስት ሐውልቱ በድንገት ለማንሳት በሞከረበት ሰዓት የአዲስአበባ ሕዝብ ያለምንም ጥሪ በመሰባሰብ ሒደቱን
የተከታተለ ሲሆን  ሐውልቱ ከተነሳ በኋላ በእንጨት ሳጥን ውስጥ ታሽጎ በሎቤይድ ተሸከርካሪ ተጭኖ ወደ ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ቅጥር ግቢ ተጓጎዞአል፡፡
በዛሬው ዕለት ረፋድ ጀምሮ ሐውልቱን ለማንሳት በተደረገው እንቅስቃሴ ወደ አ/አ ማዘጋጃ ቤትና ፒያሳ አካባቢ
ከፍተኛ የትራፊክና ህዝብ መጨናነቅ ተስተውሏል፡፡ መንግስት በሒደቱ ተቃውሞ ሊነሳ ይችላል በሚል ግምት ከፍተኛ
የፖሊስ ጥበቃ ሃይል በግልጽ፣ የታጠቁ የፌዴራል ፖሊስ አባላትን በስውር አሰማርቶ የታየ ቢሆንም ይህ ዜና
እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ተቃውሞ አልተነሳም።
የባቡሩን ግንባታ ተከትሎ የአቡነ ጼጥሮስ ሐውልት እንደሚነሳ በታወቀበት ወቅት የኢትዮጵያ ባለውለታ የሆኑትን
ሰማዕት ሐውልት ከማንሳት ለባቡሩ የዲዛይን ለውጥ ቢደረግለት ይሻላል ያሉ ወገኖች ተቃውሞአቸውን በአገር ውስጥና
በውጪ አገር ያሰሙ ሲሆን መንግስት በበኩሉ ሐውልቱ በጊዜያዊነት ተነሰቶ ግንባታው ከተጠናቀቀ በኋላ በክብር
ተመልሶ ይተከላል የሚል ምላሽ በመስጠት ተቃውሞውን ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡

አንዳንድ የገዥው ፓርቲ ከፍተኛ ሹማምንት የሕዝቡን ተቃውሞ ሐውልት ይሻላል ወይስ የድንጋይ ክምር በማለት እስከማጣጣል መድረሳቸውም የሚታወስ ነው፡፡
በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየቱን ያሰፈረው ወጣቱ ደራሲ በእውቀቱ ስዩም ሀውልቱ ሲነሳ የፈጠረበትን ስሜት ሲገልጽ ” ከጥቂት ጊዜ በሁዋላ ጋዜጠኛ ጓደኞቼ ካሜራቸውን ታጥቀው ደረሱና ተቀላቀሉኝ ሀውልቱን ማስቀረት ስላልቻሉ ምስሉን ቀርጸው ለማስቀረት ተሯሯጡ። ድንገት ቀና ብየ ሳይ ከሀውልቱ ፊት ለፊት ጅማ በር የሚባል ፣ ጣሊያን የሰራው አሮጌ ህንጻ ይታየኛል። ባቡሩ የአቡነ ጴጥሮስን መታሰቢያ ደቅድቆ ሲያልፍ፣ ጣሊያን  ሰራሹን ግንብ ንክች አያደርገውም። ጉደኛ ባቡር” ብሎአል።

በእውቀቱ ” አዲስ አበባ ከጊዜ በሁዋላ ያለጥርጥር ባቡር ይኖራታል። ቀለበት መንገዶች ይኖሯታል። አሪፍ ህንጻዎች ይኖሯታል። ነገር ግን ትናንት የሚባል ነገር አይኖራትም።ታሪክ የሌላት ከተማ የሚለው ለአዲስ አበባ የተገባ ቅጽል ነው ሲል አክሎአል።

Breaking News: TPLF sentenced Eskinder Nega and Andualem Arage


Breaking News: TPLF sentenced Eskinder Nega and Andualem Arage

ADDIS ABABA (AFP) — An Ethiopian court on Thursday dismissed the appeal of blogger Eskinder Nega and opposition leader Andualem Arage who were jailed last year for terror-related offences.
Serkalem Fasil Eskinder Nega's Wife
“I am very sad, I am very angry, I cannot talk rationally,” Eskinder’s wife Serkalem Fasil told AFP after the decision.
“The sentencing is still correct so there is no reduction,” said Supreme Court judge Dagne Melaku, confirming Eskinder’s jail term of 18 years and Andualem’s life sentence.
One of the charges — serving as a leader of a terrorist organisation — was dropped, but had no affect on sentencing.
After the ruling, Eskinder made an emotional appeal to the court which was crowded with family, friends and diplomats.
“The truth will set us free,” he said. “We want the Ethiopian public to know that the truth will reveal itself, it’s only a matter of time.”
Both men are accused of links to the outlawed opposition group Ginbot 7.
“The walls of justice will be demolished,” Andualem told AFP.
Four other men also jailed for terror-related charges had their appeal quashed.
One other defendant, however, Kinfe Michael, had his sentence reduced from 25 years to 16 years.
Rights groups have called Ethiopia’s anti-terrorism legislation vague and accuse the government of using the law to stifle peaceful dissent.
“I am very sad, I am very angry, I cannot talk rationally,” Eskinder’s wife Serkalem Fasil told AFP after the decision.
Defence lawyer Abebe Guta said that justice had not been served, and that if his clients agreed, they would appeal to court of cassation, Ethiopia’s highest court.
Who jailed Eskinder and the rest?
From left: Journalist Eskinder Nega and opposition leader Andualem Arage
Ethiopia has one of the most restricted media in the world and the highest number of journalists living in exile, according to US-based press watchdog, the Committee to Protect Journalists.
Last year Eskinder was awarded the prestigious PEN America’s “Freedom to Write” annual prize.
Rights groups including Amnesty International and Human Rights Watch condemned the initial conviction of the Eskinder in July 2012.