Tuesday, December 31, 2013

ስለ ዳግማዊ ምንሊክ የ'' ኒዎርክ ታይምስ '' ጋዜጣ (ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር) የዛሬ 96 አመት የፃፈው ፅሁፍ ለአሁኑ ትውልድ ታሪካዊ ማስረጃ ነው (gudayachin.blogspot.com)


ጉዳያችን ጡመራ ታህሳስ 22/2006 ዓም (gudayachin.blogspot.com)
ዳግማዊ አፄ ምንሊክ ፎቶ 

ኢትዮጵያ በየዘመኗ በሕልውናዋ ላይ የተቃጣባት የመበታተን አደጋን ያለፈችበት መንገድ የጦርነት መንገድ ብቻ አይደለም።ሆኖም ግን ከነበሩን የግጭት ታሪኮች በዘለለ በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ የነበሩ እና በሕዝብ ዘንድም የተወደዱ  መሪዎች ነበሩን።ከእነኝህ ውስጥ ዳግማዊ ምንሊክ አንዱ ነበሩ። አፄ ምንሊክ ሀገር የማስተዳደር ጥበብን የተማሩት በአፄ ቴዎድሮስ እጅ ሆነው እድገታቸውን በንጉሡ ቤተመንግስት ማድረግ ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ መሆኑን ብዙዎች ይስማማሉ።ንጉሡ የቀደሙ አባቶቻቸው አፄ ቴዎድሮስ እና አፄ ዮሐንስ ኢትዮጵያን አንድ የማድረግ አላማቸው እውን እንዲሆን ያደረጉ እድለኛ ንጉስም ናቸው።

አፄ ምንሊክ ኢትዮጵያን አንድ ከማድረግ አልፈው እስከ ኬንያ፣ሱዳን እና ሱማልያ ግዛት ድረስ ዘልቀው ገብተው በቅኝ ግዛት ይማቅቁ የነበሩ ህዝቦችን ነፃ ያወጣሉ የሚል ስጋት የነበረባቸው  እና በወቅቱ በእነኚሁ የጎረቤት ሃገራት  ላይ የጥቅም ፍላጎት የነበራቸው የአውሮፓ ሃገራት በብርቱ ተፈታትነዋቸው ነበር።በመሆኑም አዲስ የድንበር ውል ከኢትዮጵያ ጋር የመፈራረም ፍላጎት ከእንግሊዝ፣ፈረንሳይ እና ኢጣልያ በኩል ጥያቄ መነጻቱን የወቅቱ የታሪክ ድርሳናት ያወሳሉ።

ዛሬ ዛሬ በምንሊክ ላይ ታሪካዊ መሰረት የሌላቸው ቀድሞ አፄ ምንሊክ የቅኝ ግዛት ጥማታቸውን በገቱባቸው እና ቂም በያዙ ፀሐፊዎች የተፃፉ ናቸው ብለው ከሚነግሩን አስገራሚ ''የታሪክ'' ፅሁፎች ውስጥ ''በምኒሊክ ዘመን እስከ አስር ሚልዮን ኦሮሞዎች አለቁ'' የሚል ፅሁፍ በአንዳንድ የማህበራዊ ድህረ ገፆች ተለቀው ሲነበቡ መመልከት  አስገራሚ የሰሞኑ ክስተት ነው።በፖለቲካው አለም በቂ ርዕዮተ አለምም ሆነ ፖለቲካዊ ፍልስፍና የጠፋባቸው አንዳንድ ወገኖች ''ትርፋማ'' ብለው ያሰቡት የዘር ፖለቲካ በኢትዮጵያውያን መካከል መዝራት እና ከመቶ አመት በፊት  የሆነውን የታሪክ ክስተት የአሁኑን ትውልድ በመውቀስ ትኩረት ለማግኘት ሲታትሩ መመልከት የዘመኑ አስቂኝ ተውኔት ነው።ዳግማዊ ምንሊክ ገና ብዙ የሚጠና ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊ እና ወታደራዊ ክህሎት ባለቤት ለመሆናቸው በወቅቱ ከወጡት የዓለማችን ድንቅ ጋዜጦች አንዱ የ ኒውዮርክ ታይምስን እትም መመልከት ይበቃል።

ከእዚህ በታች በሚገኘው የኒውዮርክ ታይምስ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር እትም ላይ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ሕዝብ ብዛትን 7,000,000 (ሰባት ሚልዮን) መሆኑን ያስቀምጣል። እዚህ ላይ አንዳንድ እራሳቸውን የታሪክ ምሁራን ነን በሚል ባልተጨበጠ ይልቁንም በምኒሊክ የቅኝ ግዛት ህልማቸው ከተደናቀፈባቸው ቂመኛ ፀሐፊዎች አነበብን የሚሉት እና የኦሮምኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያንን ያማለሉ መስሏቸው  ''ምንሊክ 10 ሚልዮን ኦሮሞ ገደሉ'' እያሉ ኢትዮጵያ ከነበራት የህዝብ ብዛት (7 ሚልዮን) በላይ  ቁጥር ሲጠሩ እፍረት አልተሰማቸውም።

''ማን ያውራ የነበረ'' እንዲሉ የኒውዮርክ ታይምስ  ጋዜጣ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር እትም ላይ ጋዜጣው አዲስ አበባ በነበረ  በልዩ ዘጋቢው አማካይነት ስለንጉሡ እና ኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ሁኔታ ፅፎ ነበር።ጋዜጣው  አፄ ምንሊክ እና አስተዳደራቸውን ከገለፀበት አረፍተ ነገር  ውስጥ እነኝህ ይጠቀሳሉ  -

 - ኢትዮጵያን ወደ ህገመንግስታዊ የንጉሥ አስተዳደር ለመቀየር ሂደት ላይ መሆኗን፣

 - የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት 7 ሚልዮን መሆኑን፣

 - አፄ ምንሊክ ንጉሰ ነገስት ሲሆኑ ጦርነት የነበረው የአፄ ዮሐንስ ተተኪ  እሳቸው መሆናቸውን ካልተቀበሉት ጋር ብቻ እንደ ነበር፣

 - የአውሮፓውያንን ስልጣኔ ወደሀገራቸው ለማምጣት የባርያ ንግድን ከመዋጋታቸውም በላይ ነፃ ትምህርት ዕድል ዜጎች እንዲያገኙ መሰረት መጣላቸውን፣

 - ምንሊክ እራሱ ልዩ ችሎታ ያላቸው ሰው መሆናቸውን። ከችሎታዎቻቸው መካከል  ዲፕሎማት፣የፋይናንስ ባለሙያ እና  ወታደር የሚሉት እንደሚጠቀሱ እና

 - እንደ ዲፕሎማት እና ወታደር የጣልያንን ወረራ ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ ያደረጉበት ጥበብ መሆኑን፣

 የሚሉ ይገኙበታል።የጋዜጣውን ሙሉ ፅሁፍ ከእዚህ በታች ያለውን ሊንክ ከፍተው ያንብቡ።

 የኒውዮርክ ታይምስ  ጋዜጣ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር እትም ለማንበብ ይህንን ሊንክ ይክፈቱ።

Published: November 7, 1909 Copyright © The New York Times

http://query.nytimes.com/mem/archive-free/pdf res=F50A12F63A5A15738DDDAE0894D9415B898CF1D3 


የጃዋር መሀመድና የአንዳንድ አጨብጫቢዎች አደገኛ መንገድ በአጭሩ(ዋቅጅራ ሶሪ)

“በእናቴ መንዜና ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ነኝ፤ በአባቴ የአርሲ ኦሮሞ እና ሙስሊም ነኝ፤ ከኔ ወዲያ ለኢትዮጵያዊነት ምልክት ሊሆን የሚችል የለም” ጃዋር ይህን ያለው ከዓመት በፊት ወጣቱ ተንታኝ እየተባለ በኢሳት  በተደጋጋሚ ይቀርብ የነበረ ሰሞን ነው።

Jawar Mohamed Muslim fundamentalist
የተመቼው እና ፖለቲካዊ ንግዱ የደራለት  ሲመስለው ከኢትዮጵያውያን ጋር ተመሣስሎና አድፍጦ የቆየው ጃዋር  መሀመድ ፤በግብጽ የመንግስት ለውጥ መደረጉን ተከትሎ የሙርሲ ባለስልጣናት በአባይ ግድብ ያደረባቸውን ንዴት በግልጽ በቴሌቪዥን  ተሰባስበው እየፎከሩ በኢትዮጵያ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ሲዝ ቱ  ሰማ። የሙርሲ ባለስልጣናት  ከሰነዘሯቸው አማራጮች አንዱ፦” የኦሮሞ ነፃነት ግንባርን የሙስሊም ክንፍ ወይም ኦብነግን ማስታጠቅና መርዳት” የሚል መሆኑን የሰማው ጃዋር ሳይውል ሳያድር በአልጀዚራ ላይ ቀርቦ በግልጽ “ኦሮሞ ፈርስት” በማለት የኢትዮጵያዊነት ቆቡን አሽቀንጥሮ ጣለ። ሜንጫው ተከተለ፤የሙስሊሞችን የመብት ትግል ከኦነግ ጋር እያገናኘ ተናገረ፣ ኢትዮጵያውያን ከኦሮሚያ ይውጡ! እያለ መፈክር ሲያሰማ ተደመጠ…
እባብ ልቡን ዐይቶ እግር ነሳው እንዲሉ፤ አምላክ የሙርሲን መንግስት በአጭሩ ቀጨው እንጂ፤ የሙርሲ ሰዎች በስልጣናቸው ቢቀጥሉ ኖሮ የጃዋር መንገድ ወዴት ወዴት እንደነበር መገመቱ ቀላል ነው።
ከክፉ መንገዱ ሊመለስ ያልቻለው ጃዋር በቅርቡ በሳዑዲ አረቢያ በወገኖቻችን ላይ የደረሰባቸውን መከራ ተከትሎ በኖርዌይ የሚገኙ ተከታዮቹ “እኛ ኢትዮጵያውያን አይደለንም! ወንጀለኞች አይደለንም!” በማለት ስለወጡት እና የበርካቶችን ልብ ስላደማው ሰልፍ “ትክክል ነው” ብሎ ፃፈ። ሌላም ኢትዮጵያዊነትን የሚፃረር በርካታ ነገሮች ፃፈ፣ ተናገረ።
ጃዋር በአጭር ጊዜ እነኚህን ሁሉ ስህተቶች አድርጓል። ፈጽሟል። ኢትዮጵያዊ ነኝ ለሚል እና በትክክል ስለ አገር ምንነት ለገባው ሰው ጃዋርን ለመኮነን እና ለመለየት ከነዚህ ስህተቶች አንድኛው ብቻ በቂ ነበር። ሆኖም ከልጅነት እና ከእልክ የመጣ ስህተት ይሆናል፣ ልጁ ነገ ጧት ከስህተቱ ተጸጽቶ መንገዱን እየመረመረና እያሻሻለ ሊመጣ ይችላል፤ ይህን ልጅ ብናቀርበውና በትክክለኛው መንገድ መሄድ ቢችል በዕውቀቱ አገሩንና ወገኑን ሊያገለግል ይችላል..  በሚል እሳቤ አንዴና ሁለቴ  አልፈነዋል። ይህን ለፍቅርና አብሮ ለመኖር እንደተሰጠ ዕድል ስላየሁት ምንም አልመሰለኝም ነበር። እሱ ግን ከስህተቱ ሊመለስ አልቻለም። በተቃራኒው ጭራሽ እየባሰበት መጣ። ጃዋር  እየሄደበት ያለው መንገድ፤ ከኢትዮጵያዊነት ጋር ያለውን ርቀት አንዴ ብቻ ሳይሆን በተደጋጋሚ ዓየን።  የጃዋር ችግር ከግለሰቦችና ከፓርቲዎች ጋር ቢሆን የፈለገውን ያህል ዘመን ቢወስድ መታገሱና ማባባሉ ሊያስኬድ ይችል ነበር። ጃዋር ደጋግሞ እየወጋ ያለው ግን ኢትዮጵያዊነትን ነው። መንገዱ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ለማፈራረስ ነው። ምንም ለማያውቁ ታዳጊ ህፃናት የፈጠራ ድርሰት እየተረከ ትውልድ እየለያየ ነው። አገር በጥላቻ እንዲናጥ እያደረገ ነው።
ያደቆነ ሰይጣን ሳያቀስስ አይመለስም እንዲሉ፤ ጽንፈኛው ጃዋር በአሁኑ ወቅት ከህወሀቶች ጋር በመሆን የዓፄ ምኒልክን ምስል ከሂትለር ጋር መሳ ለመሳ እያደረገ መበተን የደረሰበት ደረጃ ላይ ደርሷል። የማንነታችን (የኢትዮጵያዊነታችን) መሰረት፤ ማላገጫና መቀለጃ  መቀለጃ ሆኗል። በበኩሌ ከዚህ በላይ በኢትዮጵያዊነት ላይ መሳለቅ ያለ አይመስለኝም። ለምን ምኒልክ ተነኩ አይደለም እያልኩ ያለሁት። ህወሀቶችም ምኒልክን ለዓመታት ሲከሱ ሰምተናል። ደግሞም ምኒልክ ይህን ፈፅሟል፣ ይህን አድርጓል.. የሚለው ክስና ወቀሳ አግባብ ያለውና ለውይይት በር የሚከፍት  ስለሆነ ችግር የለውም። ጃዋርና ተከታዮቹ ግን  ወደ አደገኛ ጽንፍ በመሄድ “ምኒልክ ሂትለር ነው” የሚል  ጸያፍ፣ ርካሽና ጨርሶ ለውይይት የማይጋብዝ ቅስቀሳ ነው እያደረጉ ያሉት።  ጃዋር በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ይህን ሲያደርግ ኢትዮጵያዊነትን፣ነፃነትን፣ ማንነትን፣ እየናደና እያፈረሰ ነው ለማለት ነው የፈለግኩት። ስለሆነም ከሰፊውና ኢትዮጵያዊነቱን ለአፍታም ተጠራጥሮ ከማያውቀው ከወንድማችን የአሮሞ ህዝብ ጋር  በፍቅርና በአንድነት መኖራችን ይቀጥላል፡፡ ወይም በግልጽ ለመናገር ያህል እኛ በኢትዮጵያዊነታችን ቅንጣት ጥርጥር የሌለን ኦሮሞዎች ከወንድሞቻችን ጋር በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር በፍቅርና በአንድነት መኖራችንን እንቀጥላለን። አገር ለማፍረስና ለመገንጠል እንዲሁም በብሔረሰቦችና በሀይማኖቶች መካከል ጥላቻና ልዩነትን ለመፍጠር ተግተው እየትቀሳቀሱ ካሉት  ከጽንፈኞቹ ከነ ጃዋር ጋር  ግን ልዩነታችን ሰፍቷልና በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ልንታገላቸው ይገባል። ከወያኔ ጋር የሚደረገው ትግል፤ ልጆቹንና ጉዳይ ፈፃሚዎቹን እነ ጃዋርን ሊያጠቃልል ይገባል። አውቀውም ይሁን ሳያውቁት በወሳኝ ሰዓት የኢትዮጵያውያንን ትግልን በማደናቀፍ የወያኔን ዕድሜ የማስቀጠል ተልዕኮ እየፈጸሙ ያሉትን እነ ጃዋርን በቸልታ ልናያቸው አይገባም።
****
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከላይ በጠቀስኳቸው ባለፉት  ሂደቶች እኔን ከጃዋር በላይ ሲገርመኝና ሲያበሳጨኝ የቆየው ታዲያ “ኢትዮጵያ አገሬ”  እያሉ ነጋ ጠባ የሚፎክሩ ሰዎች  ተግባር ነው።በተለይ አንዳንድ “አክቲቪስት” ነን የሚሉና ነፋሱ ወደነፈሰብት እየጋለቡ የሚያራግቡ  አጨብጫቢዎች፣ ነፃ ለመውጣት የምናደርገውን ትግል በመጎተትም ሆነ አገርን በማፍረስ እየተደረገ ባለው ሴራ ከጃዋር በላይ ተጠያቂ መሆናቸውን ሊያውቁት ይገባል። (ስማቸውን ያልጠቀስኳቸው ሁላችሁም ታውቋቸዋላችሁ ብዬ ነው HL & BT) ነው። ያልገባኝ ነገር  እነኚህ አክቲቪስት ተብየዎች አገር ለመገንጠል እየተጋ ካለ ጽንፈኛ ጋር የሚታከኩት ምን ትርፍ ለማግኘት ነው የሚለው ነው…  የሀገር ጉዳይ የምንሞዳሞድበት እና የምናመቻምቸው ጉዳይ አይደለም። በኢትዮጵያ ጉዳይ ቁማር መቆመርና እከከኝ-ልከክህ መጫዎት አይቻልም። ከፈለጉ ምርጫቸውን አስተካክለው ከጽንፈኛው ከጃዋር ካምፕ ይቀላቀሉ። ያ ካልተመቻቸው ደግሞ በኢትዮጵያ ባንዲራ ስም መነገዳችውን ያቁሙ።
የሀገር ጉዳይ የዕውቀት ስታንዳርድ እያወጣን  የምንሞጋገስበት፣ የምንኮፋፈስበት እና በፌስ ቡክ የምንጫዎትበት አይደለም።