Sunday, December 29, 2013

ከቴዲ አፍሮ የተሰጠ መግለጫ “ለሙዚቃ አፍቃሪዎቼ በሙሉ”


ከቴዲ አፍሮ የተሰጠ መግለጫ “ለሙዚቃ አፍቃሪዎቼ በሙሉ”
ከጥቂት ሳምንት በፊት የዳግማዊ ሚኒሊክን መቶኛ አመት የሞት መታሰቢያ ምክንያት በማድረግ በእንቁ መጽሔት ተጋብዤ ቃለ ምልልስ አድርጌአለሁኝ። ይኸዉ Ethiopian Artist Teddy Afroዉይይታችን በ “አመጣጡን ያየ አካሄዱን ያዉቃል” እርዕስ ስር ለህዝብ እንደቀረበ አዉቃለሁ። ከዚህ ዉጪ እኔ በማላዉቀዉ ሁኔታ መጽሔቱ በሰራዉ ስህተት ፎቶዬን በሌላ አነጋገር አጅቦ ያወጣዉን ከኔ እምነትም ሆን ጉዞ ጋር የሚራመድ ጉዳይ አይደለም። ይህንኑ ለማረጋገጥ “አመጣጡን ያየ አካሄዱን ያዉቃል” በሚል ርዕስ ስር በወጣዉ መጽሔት መልክቶቼን በማየት ማረጋገጥ ይቻላል። ያም ሆኖ መጽሔቱ በሰራዉ ስህተት እርምት አድርጎ ይቅርታም ጠይቆናል። ጉዞዬ የፍቅር የአንድነት እና የይቅር ባይነት ነዉና ይህንንም ጉዳይ በዚሁ ስሜት ውስጥ እናስተናግደዋለን።
ፍቅር ያሽንፋል
ቴዎድሮስ ካሳሁን

No comments:

Post a Comment