Sunday, January 24, 2016

“እኔም ሆድ ሲብሰኝ እንደዚያ ያልኩባቸው ቀናት አይጠፉም” – ቃለምልልስ ከያሬድ ጥበቡ ጋር | በኦሮሚያ፣ በሁመራ፣ በቅማንት ጉዳዮች ላይ ይናገራሉ | የቀለም ቀንድ ጋዜጣ

አቶ ያሬድ ጥበቡ ይህን ቃለምልልስ ያደረጉት ሃገር ቤት ከሚታተመው የቀለም ቀንድ ጋዜጣ ነው:: በተለይ ውጭ ሃገር ለሚገኘው አንባቢ ግንዛቤ በሚል እንደወረደ አቅርበነዋል:: 
እንደሚያውቁት ብአዴን በቅርቡ የ35ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን በተለያዩ ፕሮግራሞች ሲያከብር ቆይቷል። ከድርጅቱ መሥራቶች አንዱ ነዎትና የድርጅቱን ስኬቶችና ድክመቶች በአጠቃላይ የ35 ዓመቱን ትርፍና ኪሳራዎች እንዴት ነው የሚገመግሟቸው? ድርጅቱ ማድረግ ሲገባው ያላደረጋቸውን ነገሮች እና ወደፊት ቢሠሩ መልካም ነው የሚሏቸውን ተግባራት ጨምረው ቢገልጹልን።
የብአዴንን የ35ኛ ዓመት ምሥረታ በዓል ፕሮግራሞች ለማየት ዕድል አልገጠመኝም። የበረከትን ቃለ ምልልስ ብቻ ነው ያየሁት። የገረመኝ የሕወሓት ደጋፊዎች በመሆናቸው የሚታወቁት ወጣት ጋዜጠኞችና ጦማሪያን፣ ብአዴን በትጥቅ ትግሉ ውስጥ ተሳትፌያለሁ ማለቱ ጨርቃቸውን አስጥሎ እንደማበድ ሲያደርጋቸው ማየቴ ነበር። ጀብደኝነት ለትግሬዎች ብቻ የተሰጠ ማዕረግ አድርገው የወሰዱት ይመስላሉ። ይህን በተመጻደቁ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በኦሮሚያ ክልል ያሉ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች፣ ትጥቅ ሳያስፈልጋቸው እንኳ መጀገን እንደሚቻል አስተማሯቸው። ጦማሪያኑ ልብ ይገዛሉ ብዬ አስባለሁ። ወደ ጥያቄህ ስመልስ፣ የኢሕዴን/ ብአዴን 35 ዓመታት ትርፍና ኪሳራ እንዲህ በቀላሉ በቃለ ምልልስ የሚያልቅ አይመስለኝም። ሆኖም ልሞክር። ትልቁ ስኬት የሚመስለኝ፣ ኢሕአፓን ከሚያህል ትልቅ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ የወጣ ኢምንት ኃይል፣ ያን የጨለማ ዘመን አልፎ የሥልጣን ተጋሪ ለመሆን መቻሉ ነው። የሥልጣን ተጋሪ ስል የማይመቻቸው ሰዎች እንዳሉ አውቃለሁ። የወያኔ አሽከር መሆን ምን ያኮራል የሚሉ አሉ። እኔም ሆድ ሲብሰኝ እንደዚያ ያልኩባቸው ቀናት አይጠፉም። ሆኖም በእኔ ውሱን መረጃና ዕውቀት መሠረት፣ ባለፉት 25 ዓመታት በዘጠኙ ክልሎች ያሉትን የመልካም አስተዳደር ችግሮች ላስተዋለ፣ የተሻለ አስተዳደር ያለው የሚመስለኝ በብአዴን ሥር ያለው የአማራ ክልል የተሰኘው አስተዳደር ነው። ከሕዝቡ ጋር የተሻለ ቅርበት ያላቸው ካድሬዎች ያሉበት ክልል ሆኖ ይሰማኛል። በሙስና ደረጃም ከሌሎቹ ያነሰ ንቅዘት ያለበት ክልል እንደሆነ ነው የምሰማው። ንቅናቄውን ስንጀምር ያደረግናቸው የአምስት ወራት ውይይቶችና፣
በመጀመሪያዎቹ ዓመታት የነበረን ጥብቅ ሥነ ምግባርና ከኢሕአፓም ሰንቀን ያመጣናቸው ሕዝብና አገር ወዳድ ስሜቶች ገና ተመንዝረው ስላላለቁ ይመስለኛል።
ሌላው የኢሕዴን/ብአዴን አዎንታዊ አስተዋጽኦ የሕወሓትን ጠባብ ብሔረተኝነት እየታገለ፣ ‹‹አይዞን ይቻላል›› እያለና እያደፋፈረ፣ ነጻ የትግራይ ሪፐብሊክ ከመመሥረት፣ በአጠቃላይ ደርግን ወደመገርሰስ ትግሉ እንዲሸጋገር ያደረገው አስተዋጽኦ ይመስለኛል። በዚህም ላይ ‹‹መሃል አገር መጥተው ከሚያምሱን ቢገነጠሉ ይሻለን ነበር›› የሚሉ ድምጾች መኖራቸው ጠፍቶኝ አይደለም። ግን ትግራይና ኤርትራ ተገንጥለው ደርግን ቢተውት፣ ደርጉ፣ ደቡቡንና መሃል አገሩን እያደራጀ እንቅልፍ ይነሳቸው ስለነበር፣ ባይወዱ እንኳ ተገደው የሱማሌና ኦሮሞ አማጺያንን ወደማጠናከርና የኢትዮጵያን መበታተን ግፊት ያደርጉ ነበር። ስለሆነም የኢሕዴን መኖር ሕወሓት ተደፋፍሮ ወደመሃል አገር እንዲመጣና የአገሪቱም አንድነት እንዲጠበቅ አስተዋጽኦ ያደረገ ይመስለኛል።
የኢሕዴን/ብአዴን ድክመቶቹ ከዚሁ በመሃል አገር ሥልጣን ከመያዝ ጋር የተቆላለፉ ናቸው። በሁለት ደረጃ ነው ድክመቶቹ የሚታዩኝ። አንደኛው፣ በአመዛኙ የአርሶ አደር ድርጅት ስለነበርና፣ መሃል አገር ከደረሰም በኋላ ሊቀላቀለው ይችል የነበረው ኢትዮጵያዊ ብሔርተኛ በጥርጣሬ እንዲያየው ስለተገደደ፣ ቶሎ ብሎ የልሂቁን ድጋፍ ማግኘት አልቻለም። በአንጻሩ ሕወሓት ፊደል የቆጠረውን ትግሬ ሙሉ (መቶ በመቶ ባይሆንም) ድጋፍ ማግኘቱ፣ ቢሮክራሲውን፣ ፋይናንሱን፣ መሬቱን ፈጥኖ እንዲቆጣጠር ረድቶታል። በወቅቱ በደቡብ የአገራችን ክፍሎች፣ በተለይ በኦሮሞ ክልል በአማርኛ ተናጋሪዎች ላይ ይካሄድ የነበረውን የዘር ማጥፋት ወንጀል በመቃወም መአሕድ መቋቋሙና፣ መአሕድንም በዋነኛነት የመታገሉ ተልዕኮ ለኢሕዴን በመሰጠቱ፣ ድርጅቱ ከኅብረ ብሔራዊነቱ አሽቆልቁሎ፣ መኖሩ እንኳ አጠራጠሪ የሆነ፣ የአማራ ብሔርተኛነት ወኪልነትን ለራሱ መረጠ ወይም በሕወሓት አስገዳጅነት ተቀበለ። አመራር አባላቱ ከኤርትራ እስከ ሲዳማ የሚጣቀሱ ኢትዮጵያውያን
ያሉበት ድርጅት፣ አማራ ነኝ ሲል ‹‹ቱሪስት ብላ›› ከመባሉ ባሻገር፣ ከክልሉ ውጪ ዜጎች አማራ ናችሁ በመባል በሚደርስባቸው የንብረትና ሕይወት እጦት ሊደርስላቸው የሚችል ድርጅት ሊሆን ስላለቻለ (ቢያንስ ተቃውሞውን በመድረክ የሚያሰማ)፣ የአማራ ብሔርተኝነቱ ስማዊ (አፋዊ) ከመሆን አልፎ፣ በግድያውና መፈናቀሉ ተባባሪነት ስሙን የሚያጎድፍ ሊሆን በቅቷል። በተለይ እንደ ታምራት ላይኔ፣ ዳዊት ዮሐንስና ተፈራ ዋልዋን የመሳሰሉት መሪዎቹ የጠዋት ማታ የውግዘት መፈክራቸው ነፍጠኛ ብለው የሚጠሩት አማርኛ ተናጋሪ ሕዝብ መሆኑ፣ ለድርጅቱ መጠላትና መገለል የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል።
በሁለተኛ ደረጃ፣ ምንም እንኳን ኢሕዴን ወደአማራ ክልል አስተዳዳሪነት ቢወሰንምና፣ ከክልሉ ውጪ ባሉ አማርኛ ተናጋሪዎች ላይ ለሚደርሰው ጥቃት ተከላካይ ሆኖ ባይገኝም፣ አሁን ላይ ሆኜ ሳየው፣ ድርጅቱን የወያኔ አሽከር አድርጎ ኮንኖ የዳር ተመልካች ሆኖ ከመቀመጥ፣ ኢትዮጵያዊው ብሔርተኛው ኃይል ቢቀላቀለው ይሻል ነበር ብዬ የማስብባቸው ጊዜያት ጥቂት አይደሉም። ፖለቲካ ውስጥ ኩርፊያ መሣሪያ መሆን የሚችል አይመስለኝም። የመሃል አገሩ ሰው ከማኩረፍ ይልቅ፣ በእጁ ያለውን ይዞ (ብልጥ ልጅ እየበላ ያለቅሳል አይደል የሚባለው)፣ ብአዴንን ተቀላቅሎ ቢሮክራሲውንም፣ የባንክ ብድሩንም፣ የመሬት ቅርምቱንም እየተሻማ ቢቀጥል ይሻል ነበር ወይ ብዬ ያሰብኩባቸው ጊዜያት ብዙ ናቸው። የመሃል አገሩ ሰው ይህን ሲያደርግ፣ ኦሮሞው ደግሞ በኦነግ ዙሪያ ተመሳሳይ ተሳትፎ አድርጎ ቢሆን ኖሮ፣ ዛሬ የምናየውን የትግራይ ኤሊት እብለላ (ጥጋብ) (በትግርኛ dominance ለማለት ይጠቀሙበታል) ባላስከተለ ነበር።
ሌላው የኢሕዴን/ብአዴን ችግር ከመጀመሪያው ጀምሮ በአገውነታቸው ወይም ትግሬነታቸው ማንነት ላይ ግልጽ አቋም መያዝ ያልቻሉ ግለሰቦች በውስጡ ያሉበት መሆኑ ነው። በአመራሩ ደረጃ ታደሰ ካሳና (ጥንቅሹ)፣ ካሳ ተክለብርሃን ያ ችግር ያለባቸው ሰዎች ይመስሉኛል። ሸሪፎ (ካሳ ተ/ብርሃን)፣ ኋላ የተቀላቀለን ትንሽ ልጅ ስለነበር ብዙም አላስታውሰውም። ጥንቅሹን
ፖለቲካ ገና አልገባንም ነበር። ዓላማ፣ መስዋዕትነት፣ ቅንነት፣ ሕዝብን ማገልገል ወዘተ. ነበር አዕምሯችንን የሞላው። በችርቻሮ ደረጃ አስፈላጊ የሆነው የፖለቲካ ሀ…ሁ ገና አልገባንም ነበር። ስለሆነም ቅንነታችን ብቻውን ሊረዳን አልቻለም። የወዲ ዜናዊ ፖለቲካዊ ቁማር መመከቻ ብልሃት አልነበረንም። ስለሆነም ተበለጥን።
ከኤርትራ ሁለት ወራት የሚሞላ ጉብኝት በኋላ ወደሰቆጣ ስመለስ፣ ታደሰ ከሻዕብያ የተረከብናቸውን 300 ምርኮኞችና (ኋላ 7 ዓመታት ኢሕዴን ውስጥ ከታገሉ በኋላ ኦሕዴድን እንዲመሠርቱ የተደረጉት ኦሮሞ ኢትዮጵያውያን) መሣሪያና ገንዘብ ተረክቦ እንዲመጣ ኤርትራ ጥዬው ተመለስኩ። እግረ መንገዴን ወዲ ዜናዊ የነበረበት ወርኢ ቤዝ-አምባ ስደርስ ሊጣላኝ ነገር የሚፈልግ መለስን አገኝሁት። ከታደሰ የሬዲዮ መልዕክት ስለደረሰው ነው ብዬ አልጠረጠርኩም ነበር። ከዓመታት በኋላ ነው ታደሰና ታምራት ከወዲ ዜናዊ ጋር በድብቅ የሚገናኙበት የሬዲዮ ኮድ እንደነበራቸው ያወቅነው። ኋላ አዲስ አበባ ላይ ሥልጣን እንደያዙ የወያኔን ኤፈርት የሚኮርጅ ድርጅት ለአማራው ክልል ሲያቆሙ ታደሰን የጥረት ዋና ኃላፊ አደረጉት። በራሱ በታደሰ እምነት እንኳ ዛሬ ጥረት ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ይቆጣጠራል። የሚገርመው ግን ኤፈርት የእንግሊዘኛው (EFFORT – Endowment Fund For Rehabilitation of Tigray – የትግራይ መልሶ መቋቋም ፈንድ (ድርጅት)) ምህጻረ ቃል ሲሆን፣ ጥረት ግን የእንግሊዘኛው ኤፈርት ቀጥተኛ ትርጉም ነው። ጥረት የማን ነው የሚለውንና ብዙ የኢሕዴን ታጋዮች በየጊዜው ከድርጅቱ የተባረሩበትን ጥያቄ እንድናነሳ ያስገድደናል። የወያኔ አመራር አባላት እነርሱ በቸሩት 40 ሚሊዮን ብር የተቋቋመ ድርጅት መሆኑን ነግረውናል። ግን ታደሰ ጥንቅሹ ከላይ ተቀምጦ፣ ጥረት የሚያስገባውን ገንዘብ ለማን ነው አሳልፎ የሚሰጠው? የድርጅቱ የቁጥጥር ኮሚሸን ገቢ ወጪ ሒሳቡን ይቆጣጠረዋልን? የአማራ ክልል ፈንድ ነው ከተባለ መቼ ነው ሌጀሩን የአማራ ክልል ኦዲተር ፈትሾት የሚያውቀው? ጥያቄዎቹ ብዙ ናቸው።
የታደሰ ካሳንና የካሳ ተክለብርሃንን ጉዳይ የማነሳው  ያለምክንያት አይደለም። በብአዴን ውስጥ መሽገው፣ የወያኔ የአማራን ክልል ግፊት አስፈጻሚ ሆነው በመገኘታቸው ነው። በተለይ ከወልቃይት/ጠገዴና ሁመራ ጋር በተያያዘው የመሬት ጥያቄና፣ በቅማንት የማንነት ጉዳይ የክልሉን አመራሮች በማስጨነቅ፣ ከበረከት ቀጥሎ ጠንካራ ሚና የሚጫወቱት ሁለቱ መሆናቸውን በተደጋጋሚ እሰማለሁ። በተለይ ካሳ ተክለብርሃን ባለፉት ዓመታት ይዞት የቆየውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤነት ሥልጣን በመጠቀም፣ የወያኔ ጥቅም አስከባሪ በመሆን፣ ከአዲስ አበባ ስልክ በመደወል እንደሚያስፈራራቸው ነው ድርጅቱ ውስጥ ያሉ ከፍተኛ ካድሬዎች የሚነግሩኝ። ለመሆኑ ሕወሓት በታሪክ አጋጣሚ ባገኘው ወታደራዊ የበላይነት በኃይል የያዘውን የወልቃይት ጠገዴን ለም መሬት ሕዝብ እየገደለና እያሰረ ይዞ የሚቆው እስከመቼ ነው? ለመሆኑ በረጅም የታሪክ መስተጋብር ቋንቋውንም ሆነ ሃይማኖቱን ለውጦ ከሌላው አማርኛ ተናጋሪ ጎንደሬ ጋር የተዋሐደውን ቅማንቴ የተለየ ማንነት ጥያቄ እንዲያነሳ ለምንድን ነው ግፊት የሚደረገው? በእኔ ግምት በሰሜን ምዕራብ በኩል የትግራይ ክልል አምባገነኖች ተፈጥሯዊውን የተከዜ ወሰን ጥሰው እስከ መሃል ወገራ መጥተው ግጨው እንደደረሱ ነው የምሰማው። በእነርሱ ትንሽ ስሌት የአርማጨሆ በረሃ ብዙም ሰው ስለሌለው፣ ቀሰ በቀስ የትግራይን ችግረኛ እያሰፈሩበት ሰንብተው፣ ትግሬ የሰፈረበት መሬት ሁሉ የትግራይ ነው በሚለው አይዲዮሎጂያቸው ድጋፍ እስከ አይከል ያለውን መሬት ወደትግራይ ክልል ያጠቃልላሉ። ከዚያ ራስ ገዝ አስተዳደር የተሰጠው የቅማንት ሕዝብ ሕዝበ-ውሳኔ በማድረግ ከትግራይ ጋር መቀላቀልን ይመርጣል። አንዲት ጥይት ሳይተኮስ ጎንደር ከተማ በር ላይ ከች አሉ ማለት ነው። በነርሱ ትንሽ አእምሮ ያሰሉት እንዲህ ይመስለኛል። በትዕግስትና ፍርሃት መሃል ያለው ልዩነት የገባቸው አይመስለኝም። ቆስቁሰው ቆስቁሰው ጎንደር ብረቱን ይዞ እንዲወጣ አስገድደውታል። ይሄኛው ትውልድ ያባቶቹን ርስት ማስመለስ ባይችል ጥያቄውንና ትግሉን ለቀጣዩ ትውልድ አውርሶ ያልፋል እንጂ ጥያቄው ከቶም አይሞትም። ያልገባቸው ይህ የመሬት ምዝበራ ጦስ፣ በአዲስ አበባ ካካሄዱት ነቀላና፣ በክልሎች ከሚያካሂዱት የመሬት ነጠቃ ጋር ተዳብሎ፣ የመጨረሻቸው መጀመሪያ ሊሆን መቻሉን ነው። እንደዚያ ግን የግድ መሆን አልነበረበትም።
አፐታይታቸውን ቀነስ አድርገው፣ የሕዝቡን ዋይታ የማድመጥ አማራጭ አላቸው። ዛሬ የሚመኩበት ደህንነትና መከላከያ የቁርጡ ቀን ሲመጣና መግደል ሲሰለቸው፣ አሁንስ አብሬያችሁ አልወድቅም በማለት አፈሙዙን እንደሚያዞርባቸው ወይም እንደሚበታተን መረዳት አለባቸው። ሩቅ መሄድ የለባቸውም፤ 1966ንና የራሳቸውን 1983 ሁኔታ መለስ ብለው ማየት ነው። በወታደራዊ ኃይል ስላሸነፉ ብቻ ሳይሆን (ከደብረ ታቦር ውጊያ በኋላ ትግራይ ነጻ ከወጣ ለምንድን ነው ለሌላው የምንሞተው ወደአገራችን መልሱን ብሎ የከዳቸውን 30ሺህ ጦር ልብ ይሏል)፣ የደርጉ ወታደር ሊከላከላቸው ፈቃደኛ ስላልሆነም ጭምር መሆኑን ያውቁቱል። የቱ ጋ ነው የ‹‹ዲየን ቢየን ፉ››ን የመሰለ ወሳኝ ውጊያ ማድረግ የተገደዱት?
ስለሆነም፣ ወታደራዊ ትምክህቱን ትተው የሕዝቡን ልቦና ማድመጡን ቢመርጡ ይሻላል ባይ ነኝ። ከነዚህ የሕዝብ ጥያቄዎች ሁለቱ፣ የትግራይን ክልል ወሰን ከተከዜ ወንዝ በስተምሥራቅና በስተሰሜን መወሰንና፣ የኢትዮጵያን አርሶ አደሮች ከመንግሥት ጭሰኝነት አላቆ የመሬት ባለቤትነታቸውን ማረጋገጥ ቀዳሚዎቹ መፍትሔ የሚሹ ጉዳዮች ይመስሉኛል። የቅማንት ራስ- ገዝ አስተዳደር ለመመሥረትም ከሚያደርጉት ሙከራ ቢቆጠቡ ውጥረቱን ያረግበው ይመስለኛል። ብዙሃኑ ሕዝብ ያለፈውን የጋራ ታሪክና የነገውን ሁኔታ አርቆ አስቦና ገምግሞ አሰላለፉን ከወገኑ ጋር ያደረገ መሆኑ ግልጽ ቢሆንም፣ በሕወሓት ተደነባብረውና በጊዜያዊ ጥቅም ተለክፈው ሕዝቡን ለመከፋፈል የሚሠሩት ወገኖች ስላሉ እነዚህ አካላት አቋማቸውን መልሰው መላልሰው መመርመር አለባቸው። ሕወሓት የትግራይ ሪፐብሊክ ለማቆም ዕቅድ በነበረው ወቅት ከሱዳን የሚያዋስነው መሬት ሲፈልግ ተገጥሮአዊውን የተከዜ ወንዝ ተሻግሮ የጎንደርን መሬት የኔ ነው ብሎ ወረረ። አሁን ወልቃይቴዎች ትግሬ አይደለንም አማሮች ነን ሲሉ የግድ ትግሬ ትደረጋላችሁ የሚል የዕብሪት ፖሊሲ ከሚከተል፣ የወልቃይትን ጎንደሬነት ተቀብሎ አስተዳደሩን ለጎንደር ቢለቅ ተገቢ ነው። ከዚህም አልፎ ሄዶ፣ አንድ ቀን ሕወሓት ሲከፋው ይጠቀምበታል ተብሎ የተቀመጠውን የመገንጠል መብት ከሕገ መንግሥቱ ሰርዞ አገሬው ኢትዮጵያዊመቱን ተቀብሎ እንዲረጋጋ ማድረግ አላስፈላጊ ከሆኑ የማንነት ጥያቄዎች መነሳትና ያን ለማብረድ ግድያ ከመፈጸም ያድነዋል። የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ምሬት እየበዛ፣ ጥያቄውም እየገፋና እየተጠነከረ መጥቷልና እንደከዚህ ቀደሙ በግድያና በእስር እንፈታዋለን ማለቱ ውድ ዋጋ ያስከፍላል። በተጨማሪም፣ ሕወሓት ባለፉት 30 ዓመታት የወልቃይት መዘጋ ወይም ቆላ ላይ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ትግራውያን ስላሰፈረ፣ በጉልበት አልያዝኩም ብትፈልጉ በሕዝብ ድምጸ ውሳኔ ወይም ሪፍረንደም ቢል ወልቃይቴው መቀበል አይኖርበትም።
ማነው በሕዝበ ውሳኔው የሚሳተፈው? ማንስ ነው በፍትሐዊ መንገድ መካሄዱን የሚያየው የሚል ጥያቄ ማንሳት ይኖርባቸዋል። ፍትሐዊ ድምጸ ውሳኔ ከመደረጉ በፊት በጉልበት የገቡት የሕወሓት ካድሬዎች ወደትግራይ ተመልሰው አስተዳደሩ ወደ ጎንደር መካለል ይኖርበታል። ለተወሰኑ ዓመታት የማረጋጋት ሥራ ከተካሄደ በሁዋላ ብቻ ነው አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የሪፍረንደም ጥያቄ ሊነሳ የሚችለው። አሁን አይደለም።
ወደፊት ቢሠሩ መልካም ነው ከምላቸው፣ ቀዳሚው የሚመስለኝ፣ ኢሕአዴግ በውስጡ የሐሳብ ድርቀት የሚያጠቃው ድርጅት እየሆነ ስለመጣ፣ ሐሳብ ከውጪ ለመቀበል የሚችልበትን ሁኔታ ማመቻቸት ይኖርበታል። አንዱ መንገድ ፕሮፌሽናል መደቡንና ካድሬውን መለየት፣ መንግሥትንና ፓርቲውን መለየት የግድ ይመስለኛል። መንግሥት የሁሉም ዜጎች የጋራ ተቋም መሆኑን በመረዳትም (መንግስት የሚቆመው በሕዝቡ አሥራት ወይም ታክስ እንጂ በፓርቲ አባላት መዋጮ ስላልሆነ)፣ የመንግሥት ሥራ ለሁሉም ዜጎች ክፍት የሆነና፣ ሥራ ለማግኘት የፓርቲ አባልነት አላስፈላጊ መሆኑን በመቀበል፣ በ1997 ዓመተ ምህረቱ ምርጫ ተደናብረው የገቡበትን የማንአለብኝነትና የወመኔ አሠራር መቀየር ይኖርባቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ማድረግ መቻል አለባቸው ወይም ይህን መሠረታዊ ጉዳይ ማስፈጸም ካልቻሉ በፈቃዳቸው ሥልጣናቸውን ቢለቁ መልካም ነው እላለሁ። አንባቢዎችህን እንዳላሰለች እዚህ ላይ ላቁም።
ኢሕአዴግ ኢትዮጵያ ውስጥ ብሔራዊ መግባባት እና ዴሞክራሲያዊ አንድነት ተፈጥሯል ይላል። አገዛዙ ይህን ይበል እንጂ ደግሞ በሕዝቦች መካከል ከፍተኛ የሆነ አለመተማመንና ጥርጣሬ ነው ያለው። በብዙ አካባቢዎች የብሔረሰብ ግጭቶች አሉ፤ ዜጎች በተለይ አማሮች በሰፊው ይፈናቀላሉ። በእርስዎ ግምገማ ሁኔታው ወደ አደገኛ የዘር ፍጅት እንዳያመራና የኢትዮጵያን ህልውና እንዳይፈታተን መደረግ አለበት የሚሉት የመፍትሔ ሐሳብ ምንድነው? ብሔራዊ መግባባትና አንድነት ሊመጣ የሚችለውስ እንዴት ነው?
አማሮች ይፈናቀላሉ ላልከው እርግጠኛ አይደለሁም። አማርኛ ተናሪዎች ማለቱ ሳይሻል አይቀርም። ትላልቆቹ፣ እንደ ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌና መስፍን ወልደማርያም ያሉ ሰዎች የአማራ ብሔርን መኖር ሲጠይቁ ማድመጡ የተሻለ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ጎንደሬዎች፣ ጎጃሞች፣ ወሎዬዎች ናቸው የሚታዩኝ። አማሮች ገና ከስንት አበሳና የመሬት ግፊት በኋላ የሚፈጠሩ ነው የሚመስለው። እንደ ትልቅ ፍጻሜ ካየነው፣ አማራነት ከወያኔ ምሬት የተረገዘና ገና በጽንስ ላይ ያለ መስሎ ነው የሚሰማኝ። ወደፊት መወለዱንም እርግጠኛ አይደለሁም። ምነው ሸዋን ረሳኸው ብትለኝ፣ ሸዋ አማርኛና ኦሮሞኛ ተናጋሪ ከመሆኑም በላይ፣ እርስ በርሱ በጣም የተዳቀለ፣ በባርነት ይዟቸው ከነበሩ የቤት አገልጋዮቹ ጋርም የተዋለደ በመሆኑ፣ የዘመናዊት ኢትዮጵያ ጦረኛ ስለነበር ቀዳሚ ማንነቱ ኢትዮጵያዊ ይመስለኛል። አማራ ነህ ብትለው ይከፋዋል፤ አይቀበለውም። ከአማራ ክልል ውጪ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ግን በየዕለቱ ግፍ የሚወርድበት አማራ ነህ ተብሎ ስለሆነ፣ ሳይወድ በግዱ አማራ እየተደረገ ሳይሆን አይቀርም። ራሱን ለመከላከል ሲልም፣ ሕይወቱን ጠብቆ ለማቆየት እንደ አማራ መሰባሰብ ይገደድ ይሆናል። ምናልባት የአማራ ብሔርተኝነት የሚወለደው፣ ከክልሉ ውጪ ባሉት የቋንቋው ተናጋሪዎች ሊሆን ይችላል። መገፋት የወለደው ብሔርተኝነት።
ለአማርኛ ተናጋሪዎች በየክልሉ ተጠቂ መሆን ትልቁን አስተዋጽኦ የሚያደርገው ሥርዓቱ ዘር ተኮር ቅኝት ያለው በመሆኑ የማንነት ጥያቄ እንዲጎላና፣ ኢትዮጵያዊ ማንነት ሁለተኛ ደረጃና ከዚያም ያነሰ መገለጫ እንዲሆን ለ25 ዓመታት ያደረገው ግፊት ውጤት ነው። ከትግራይ ቤዛቸው ብዙ ርቀው ስለመጡና ቁጥራቸውም አነስተኛ በመሆኑ፣ ኢትዮጵያዊነትን በማዳከምና ብሔረሰባዊ ማንነት እንዲጎለብት አገሬውን ሁሉ በማነሳሳት፣ በተለይ ኢትዮጵያዊነትና የኦሮሞ ብሔርተኝነት ተገዳዳሪ ኃይሎች መስለው እንዲቀርቡ በማድረግና፣ ኢትዮጵያዊነትን እንደ አማራ ትምክህት በማንቋሸሽ የፈጠሩት የአገዛዝ ዘይቤ ነው በጥያቄህ ያነሳኸውን የርስ በርስ የመተላለቅ አደጋ የጋበዘው። ትልቁም መፍትሔ መንግሥትና ገዢው የፖለቲካና ቢዝነስ ኤሊት የያዙት መንገድ ወደጥፋት የሚወስዳቸው መሆኑን አውቀው፣ እስካሁን የመጡበት መንገድ ያደረሳቸውን የገደል አፋፍ ማየት ነው። በዚሁ መቀጠል ከፈለጉ ከማይፈሩት ገደል ውስጥ መውደቃቸው አይቀርም። ብቻቸውን የሚወድቁ ቢሆን ባልከፋ ነበር። ሆኖም አገራችንን ጭምር ይዘው ስለሚወድቁ አብረን መምከር የግድ ነው። አብሮ ለመምከርም እስካሁን ከሚያሳዩት የማፊያ ዝንባሌ መታቀብ አለባቸው። እኛ ከወደቅን ትበታተናላችሁ ስለሆነም ሰጥ ለጥ ብላችሁ ተገዙ ከሚለው ሟርታቸው ተቆጥበው፣ እንዴት ነው ለሁላችን የምትመች አገር መገንባት የምንችለው የሚል መድረክ መክፈትና ሕዝቡንና በተለይ ምሁሩን ማወያየት ይኖርባቸው ይመስለኛል። በር ዘግተው የሚደርጉት የፓርቲ ጉባኤ መፍትሔ ሊሆን እንደማይችል የደረሱበት አፋፍ ሊያሰተምራቸው ይገባል እላለሁ። ከኢሕአዴግ ውጪ ያለውን ድምጽ ማድመጥ ይገባቸዋል።
እንደሚታወቀው ባለፈው ብሔራዊ ምርጫ ኢሕአዴግና አጋሮቹ መቶ በመቶ አሸነፍኩ ማለቱንና የፖለቲካ ከባቢው ከጊዜወደ ጊዜ እየጠበበ መምጣቱን ተከትሎ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት አልቆለታል፤ ከዚህ በኋላ ለውጥ ሊመጣ የሚችለው በኢሕአዴግ ውስጥ ሊፈጠር በሚችል ችግር/ክፍፍል ብቻ ነው የሚሉ አስተያየቶች እየተደመጡ ነው። የኢትዮጵያን ፖለቲካ በቅርብ እንደሚከታተል አንጋፋ ፖለቲከኛ የአገራችንን የፖለቲካ ሁኔታ እንዴት ይገመግሙታል? ኢትዮጵያ ከዚህ አረንቋ ልትወጣ የምትችለውስ እንዴት ነው?
አገዛዞች ሁሉ የሚወድቁት ራሳቸውን ለማረም ፈቃደኛ ስላልሆኑ ነው። ያልተገደበ ሥልጣን ስላላቸው፣ በአገሪቱ ውስጥ የፍርሃት ጥላ እንዲያጠላ ያደርጋሉ። ስለሆነም የሕዝቡን ተስፋ፣ ፍርሃትና ተቃውሞ የሚያውቁበት መንገድ የለም። ካድሬ ባጦዘው ሪፖርት ነው አገሩን የሚያዩት። በዚህ ላይ ተገዢው ሕዝብ ደግሞ እንደ ኢትዮጵያ ሕዝብ ዓይነት የሺህ ዓመታት አገዛዝን የመሸከም የደነደነ ጫንቃ ያለው ሕዝብ ሲሆን ገዢዎቹ ይሰክራሉ። የሕዝብ ድጋፍ አለን ብለው ራሳቸውን እስኪያሳምኑ ድረስ ተላላ ይሆናሉ። በአንጻሩ፣ ቢጠይቁት እንኳ እውነቱን የማይነግራቸው ሕዝብ ግን ወደውስጥ እያቄመ ነው። አድብቶ ምቹ ጊዜ ነው የሚጠብቅላቸው። ቀኑ ሲደርስ ‹‹የሰከረ አሳ አመለጠህ፣ በለው!›› ይልና ከቀፎው እንደተለቀቀ ንብ መናደፍ ይጀምራል። አይጣል ነው። እንዲህ ዓይነት ሕዝብ ገዢዎቹን የሚያዘናጋውን ያህል፣ ሊመሩት የሚችሉትንም ልጆቹንም ተስፋ ያስቆርጣል። በመሆኑም ሁሌም፣ ተገቢው አመራርና ድርጅት ስለማይኖረው፣ ‹‹ሆ!›› ብሎ በተነሳበት ቅጽበት የሚከፍለው መስዋዕትነት ትልቅ ቢሆንም፣ ውጤት አልባ ለመሆን ይገደዳል። ወጣት ልጆቹን ገብሮ፣ ያነባው እንባ ሳይደርቅ፣ በአዲስ መልክ ሊገዙት የሚሸነግሉትን አዲስ ገዢዎችን ይፈለፍላል። ስለሆነም፣ የፍትሕና ነጻነት ቀን ትርቅበታለች። ይህ ሁኔታ ካልተለወጠ የኢትዮጵያ የነጻነት ብርሃን እንደራቀን ይኖራል።
በተራዘመ ሠላማዊ ትግል ልምድና ድርጅት ያካበተ ሕዝብ፣ አገዛዝን የመቋቋም አቅም ይገነባል። በመጨረሻም በማያዳግም መንገድ ማንበርከክ ይችላል። በአንጻሩ በጥቂት ጀግኖችና የጎበዝ አለቆች (ለነርሱ ያለኝ አክብሮት እንደተጠበቀ ሆኖ) የሚተማመን ሕዝብ ግን፣ የጎበዝ አለቆቹ ጭፍራ ከመሆን ላይድን ተረግሟል። ኢትዮጵያችንንም ሰንጎ የያዛት፣ ለውጥ የማምጣቱ ኃላፊነት ለጥቂቶች ምርጦች የተተወ በመሆኑ ነው። እነዚህ ጥቂቶች ግን ምን መልአክነት የደረሰ ንጽሕና ቢኖራቸው፣ በአንድ በኩል ቁጭ ብሎ የሚጠብቅ ሕዝብ፣ በሌላ በኩል የሙስናና ንቅዘት ልምድ ያካበተ ነጋዴና ባለሀብት መደብ ባለበት ሁኔታ፣ ሚዛኑ ሁሌም ወደኋለኞቹ ማድላቱና፣ መልአክነት የሚጠበቅባቸው መሪዎችም ፈጥነው የሚዘቅጡበት አደጋ ሰፊ ነው። ደርጉንና ኢሕአዴግን ማየት ነው። ታዲያ ምን ይሻላል? የጨነቀ ነገር ነው።
እርግጥ ነው ኢሕአዴግ ውስጥ ያለ ክፍፍል ሊረዳ ይችላል። ሆኖም የገዢው ኃይል ለመከፋፈል በመጀመሪያ በሕዝብ ትግል የተንገላታ መሆን አለበት። ሥልጣናችንን በምን መንገድ እናስቀጥል በሚል ጉዳይ ላይ ነው ገዢዎች የሚከፋፈሉት። ይህ የሚሆነው ደግሞ የሕዝቡ ሰላማዊ ትግል ፋታ የማይሰጥ፣ አጣዳፊ ምላሽ የሚጠይቅና የሚያስፈራ ሲሆን ነው። ይህ ከግብታዊ የሕዝብ ሰላማዊ አመጽ ሊገኝ የመቻሉን ያህል (ቱኒዚያን ማየት ነው)፣ በአብዛኛው ግን ውጤቱ ቀደም ብዬ ለማሳየት አንደሞከርኩት፣ አንዱን አገዛዝ በሌላ ከመተካት ውጪ አቅም አይኖረውም (ግብጽን ማየት ነው)። ይህም ቢሆን ግን፣ ተሞክሮው ሕዝቡን አስተምሮት የሚሄደው ልምድ ትልቅ ስለሆነ፣ ዝም ብሎ ከመገዛት በግብታዊነት አምፆ የወደቀ ሕዝብ ይሻላል። የሚያስተሳሰረው የጋራ ተግባርና የሚኮራበት የመስዋዕትነት ታሪክ ይኖረዋል። ብዙ ወጣቶች ይሞቱ ይሆናል፣ ግን በጫት ደንዝዘው፣ በድህነት ተቆራምደው፣ ወይም ይህን ሲሸሹ አሳ ነባሪና ‹‹አይሲስ›› የሚባል አውሬ ከሚበላቸው፣ ታሪክ ለመሥራት ሕይወታቸውን የገበሩ ወጣቶች ለቤተሰባቸውም ሆነ ለአገራቸው የሚያኮሩ ናቸው። ለዚህ ተገቢውን ክብር ለመስጠት ግን የታደልን መስሎ አይሰማኝም።
ለምን ይሆን በድህነት፣ በበሽታ፣ በረኀብ፣ በሥራ አጥነት መሞትን ለሕዝብ ፍትሕ ሲባል ከተከፈለ መስዋዕትነት አብልጠን የምናየው? አንዱ ችግር የሚመስለኝ፣ ለኔ ትውልድ መስዋዕትነት የሚሰጠው ትርጉም ነው። የየካቲት 66 ወጣቶችና ምሁራን ደም እንደ ደመ-ከልብ ነው የታየው። አዲሱን ሥርዓት ማዋለድ ሲያቅተን አሮጌውን መመኘት ያዝን። ስለሆነም፣ አሮጌውን ያፈረሱትን በጠላትነት አየናቸው። በተለይ በደርግ ዘመን ያደገው ወጣት፣ ታላላቅ ወንድሞቹን ከመኮነን ከማላዘን ውጪ ወይ የኔ የሚለው ሐሳብም ሆነ ተግባር የለው፣ ወይ ተሸናፊነቱን ተቀብሎ አርፎ አይቀመጥ፣ የተደረገውን ትግል ሲያንቋሽሽ ራሱ ወደ አርባዎቹ መጨረሻና ሐምሳዎቹ መጀመሪያ እየደረሰ ነው። ደስ የሚለውና ተስፋ የሚሰጠው ግን በኢሕአዴግ ዘመን የተወለዱትና ያደጉት ወጣቶች የኔን ዘመን ወጣቶች ታታሪነትና ጀግንነት የሚስተካከል ብስለት ማሳየት ጀምረዋል። የዞን ዘጠኝ ጦማሪያንን፣ የሚዲያ ጀግኖቻችንን፣ እንዲሁም ከተመክሮ ማነስ የሚፈጠሩት ስህተቶች እንደተጠበቁ ሆነው የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችን እና በሰሞኑ የኦሮሚያ ክልል በመሬት ባለቤትነት ጉዳይ ላይ በሰላማዊ ትግል አገር ያናወጡትን ወጣቶች ማየት ነው። ጽናታቸው፣ ቁርጠኝነታቸው ተስፋ የሚሰጥ ነው። ማሸነፍ ሲችሉ ተስፋ ቆርጠው አገር ጥለው ለመሰደድ እንዳይከጅሉ የኢትዮጵያ አምላክ ልበ ብርሃን ይስጣቸው። ከተሰደዱ ግን ይህ ሁሉ ድካምና እንግልት ውኃ ሊበላው ነው። በአገር ውስጥ ቆይተው ሰላማዊ ትግሉን ከዳር ያደርሳሉ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።
ወደ አዲስ አበባ ጉዳይ እንምጣ። አገዛዙ የአዲስ አበባና የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ ማስተር ፕላን ሁሉንም አካባቢዎች በጋራ ለማልማት እንዲጠቅም ሆኖ መዘጋጀቱን ሲገልጽ፤ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ማስተር ፕላኑን ይቃወሙታል። ብዙ አዲስ አበባን እድገት የሚፈልጉና የሚደግፉ ኃይሎች በአንጻሩ የኢሕአዴግን የመሬት ዝርፊያና አርሶ አደሮችን መፈናቀል ቢቃወሙም አርሶ አደሮች የሚቋቋሙበት መንገድ ተፈልጎ አዲስ አበባ ተፈጥሯዊ እድገቷን መቀጠል አለባት ይላሉ። በእርስዎ አስተያየት የአካባቢውን አርሶ አደሮች ሳይጎዳ የአዲስ አበባ እድገትና ዘላቂ ልማት ሊቀጥል የሚችለው እንዴት ነው?
ኢሳት ቴሌቪዥን ላይ ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ በዚህ ሰሞን የሰጡትን ቃለ ምልልስ አድምጠህ ከሆነ፣ ውብና ቀለል ባለ ቋንቋ ነው ችግሩን ያቀረቡት። የከተማ ክልል ሰፍቶ ወደገጠር ቀበሌዎች ሲቃረብ የአርሶ አደሩ እልልታ ከሩቅ ይሰማል፤ ምክንያቱም በጋሻና በሔክታር እየተለካ ይሸጥ የነበረው መሬቱ በሜትርና በስንዝር እየተለካ ስለሚሸጥ አርሶ አደሩ ሀብታም ይሆናልና ነው። ስለሆነም የከተማውን መስፋፋት በዙሪያው ያለው አርሶ አደር በናፍቆት የሚጠብቀው ነገር ነው። በአዲስ አበባ ዙሪያ ያሉ አርሶ አደሮች መርሐ ግብሩን የተቃወሙት ከመሬታቸው ይነቀላሉ እንጂ የሽያጩ ተጠቃሚ ስለማይሆኑ ነው። ስለሆነም ጥያቄያቸው ተገቢና የሚደገፍ ነው ነበር ያሉት ታላቁ ምሁር። የኔም አስተሳሰብ ተመሳሳይ ነው። የሰሞኑ የሕዝብ ተቃውሞ እምብርት ጥያቄ የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ ነው።
የምጨምረው ነገር ቢኖር ይህን የመሬት ጥያቄ ከማንነት ጥያቄ ጋር ማቆላለፍ የሚፈልጉት የኦሮሞ ብሔርተኞች ሁሉ የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነት መብት አይቀበሉም። ልክ እንደ ኢሕአዴግ ሁሉ፣ እነርሱም አርሶ አደሩ የመሬቱ ባለቤት ከተደረገ፣ በርካሽ ቸብችቦ ይደኸያል ብለው ይፈራሉ። የኦሮሞ አርሶ አደር መሬት አልባ ሆኖ ይደኸያል ብቻም ሳይሆን፣ የአማራ ሀብታም ይገዛዋል ብለውም ይፈራሉ። የአማራ ሀብታም የተደመሰሰ መሆኑ አይታያቸውም። በደርጉም ሆነ በኢሕአዴግ 40 ዓመታት ሙሉ አበሳውን ያየ በመሆኑ የሚፈሩት የሌለ ነገርን ነው። ዘመኑም ተቀይሯል። ዕድሜ ለእሌኒ ገብረመድህንና ለሴልፎን ቴክኖሎጂ፣ እንኳንስ በአዲስአበባዙሪያያለአርሶደር፣ባሌጠረፍላይያለ እንኳ በቆሎውን ለመሸጥ፣ ‹‹ሃሎ አዲስ አበባ!›› ብሎ የገበያውን ዋጋ አጣርቶ እንደሚሸጥ ነው በተደጋጋሚ የምሰማው። ስለሆነም፣ አርሶ አደሩ ጥቅሙን አያውቅም፣ መሬቱን በርካሽ ዋጋ ሸጦ ይደኸያል የሚለው ስጋት ቦታ ሊኖረው አይገባም።
በተግባር እንደምናየው አርሶ አደሩ የመሬቱ ባለቤት ሳይሆን ሲቀር ብቻ ነው፣ የደላሎችና የመንግሥት ባለሥልጣን ሸሪኮቻቸው መጫወቻ ሆኖ ፍጹም ድህነት ውስጥ የሚወድቀው። የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ ግን ከአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ባሻገር የፍትሕና ነጻነትም በር ከፋች ነው። ሕዝቡን ሌላ መተዳደሪያ ክህሎት ሲያጣ ካድሬ በመሆን፣ ለባለሥልጣናት ጭራውን እየቆላ ሕዝቡን አበሳ ከሚያሳየው የፓርቲ አባል ፍርሃትና ጭቆና ነጻ ያወጣዋል። አርሶ አደሩ ከመሬት ባለቤትነቱ ጋር ሰብዕናውም ብቻ ሳይሆን፣ በሕይወቱ ላይ አዛዥ ናዛዥ መሆኑን ይረዳል። ስለሆነም፣ ኃላፊነትንና ዜግነትን፣ ከዚህ ጋርም በተጣመረ ለቤተሰቡና ለአገሩ መቆርቆርን መሰዋትን ያመጣል። የተጠባባቂነትን ባህል በማስወገድ፣ በሌላ የማላከክን ደካማነት በማጥፋት ለጠፋውም ሆነ ለለማው የግል ተጠያቂነትን ያዳብራል። የመንግሥት ባለሥልጣናትም በቀላሉ የማያስደነብሩት ዜጋ ይሆናል። ይህ ዜጋ ሲፈጠር ብቻ ነው ስለ ዴሞክራሲና የሕግ ልዕልና ማውራት የምንችለው። ስለሆነም ከመሬት ባለቤትነት ጋር የተቆራኙትን መልከ ብዙ አገራዊ ፋይዳዎች በማየት፣ የኦሮሞ ብሔርተኞች በዚህ ማዕከላዊ ጥያቄ ላይ ከገዢው ፓርቲ የተለየ አቋም እንዲይዙ፣ ሕዝቡም ፓርቲዎቹ ይህን አቋም እንዲይዙ ግፊት እንዲያደርግባቸው ጥሪ ማድረግ እወዳለሁ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወጣት ጃዋር መሐመድን የመሰሉ የኦሮሞ ብሔርተኞች፣ የአዲስ አበባን መስፋፋት አንቃወምም፤ ሆኖም አርሶ አደሩ ተገቢውን ካሳ ማግኘት አለበት ማለት መጀመራቸው የአስተሳሰብ እድገት ነው እላለሁ። ግን ከካሳ ባሻገር የአርሶ አደሩን ቀጥተኛ ተጠቃሚነት የሚያጠናክረውን የመሬት ባለቤትነቱን መብት ቢቀበሉና ትግሉን ቢያጠናክሩ የነጻነት ቀን የበለጠ የሚቀርብ ይመስለኛል። በተመሳሳይ መንገድ ባለፉት 25 ዓመታት አዲስ አበባ ውስጥም ከይዞታው እየተፈናቀለ በከተማው ዳር ወዳሉ ቀበሌዎች የተወረወረውን የአዲስ አበባ ነዋሪ ትግሉን እንዲቀላቀል የሚያስተባብረው ይሆናል። የመሬት ባለቤትነት ጥያቄው ተሰልቦ የማንነት ጉዳይ ተደርጎ ሲቀርብ ግን፣ ለፍርሃትና ለጥርጣሬ ቦታውን በመተው፣ የትግል ኅብረት እንዳይኖር ያግዳል። ይህን ማየት ለምንድን ነው የሚከብደው?
ይህ ጽሁፍ የተገኘው ከዘ-ሐበሻ ድህረ ገጽ ነው።

Sunday, January 17, 2016

የዶ/ር መረራ የቡዳ ፖለቲካ እና መቀበል ያቃተው መራራ እውነት – ግርማ ሠይፉ ማሩ

ዶክተር መረራ “የኢትዮጵያ የታሪክ  ፈተናዎች እና የሚጋጩ ሕልሞች” በሚል አዲስ መፅኃፍ አስነብቦናል፡፡ በአንድ ጋዜጣ ላይ የዶክተር መረራ ከዮኒቨርሲቲ መሰናበት ያመጣው አንድ በጎ ጎን መሆኑን አንብቤያሁ፡፡ እኔም በዚህ እስማማሀለሁ፡፡ ብዙ የሀገራችን ፖለቲካኞች ጋዜጠኛ መቅረፀ ድምፅ ይዞ በሚጠይቃቸው ጥያቄ መልስ ከመስጠት የዘለለ ብዕርና ወረቀት አገናኝተው የሚያምኑበትን የፖለቲካ መስመር እና በግላቸው ያላቸውን ምልከታ ማካፈል ይቸግራቸዋል፡፡ የዶክተር መረራ ከዚህ በፊትም በተመሳሳይ ለንባብ ያበቃው መፅኃፍ ጋር ይህን መፅኃፍ ሲጨመርበት ቢያንስ በፖለቲካ መስመሩ ላይ ግልፅ መረዳት እንዲኖረን ያደርጋል፡፡ ለዚህ ፅሁፍ መነሻ የሆነኝ ግን በዋነኝነት ዶክተር መረራ አውቆ የሚዘላቸው አንድነትን የሚመለከቱ ጉዳዮች ሲሆኑ እግረ መንገዴን ከመፅኃፉ የተረዳሁትን ለማካፈል ጭምር ነው፡፡
ዶክተር መረራ በእኔ መረዳት ዛሬም መኢሶን ነው፡፡ በተቻለው መጠን መኢሶን በመከላከል እና ዋናውን ጥፋት በደርግና ኢህአፓ ትከሻ ላይ ሲጭን ነው የሚታየው፡፡ መቀበል ያቃተው መራራው እውነት መኢሶን ከደርግ ጋር ተባብሮ የደርግን ጡንቻ ማፈርጠሙ ከዚያም ተከትሎ ለተፈጠረው ጥፋት ድርሻውን ማንሳት እንዳለበት በግልፅ ሊያሳየን አለመቻሉ ነው፡፡ ድርሻ መውሰድ ስል ጥፋትን አምኖ ይቅርታ መጠየቅ እና ለእርቅ ዝግጁ መሆን ማለቴ ነው፡፡ በእኔ የፖለቲካ እሳቤ ውስጥ ሂሳብ ማወራረድ የሚል የለም፡፡
ዶክተር መረራ አሁን ኢትዮጵያ የምንላትን ሀገር ቅርፅ ያሲያዙትን ምኒሊክን ጀግንነት በጥያቄ ምልክት ውስጥ በማስገባት እና ከሶማሊያ ጋር አብረው ሀገር ሲወጉ ነበር የሚባሉትን “ዋቆ ጉታን” ጀግና እያደረገ በአክራሪ ኦሮሞ ብሔርተኞች ድጋፍ የመሻት ፍላጎቱን በመፅሃፉ ውስጥ ታዝቢያለሁኝ፡፡ ዶክተር መረራ ወደ መሃል እንምጣ እያለ ጥግ ጥጉን የሚሄድ መሆኑን ማሳያም ጭምር ነው፡፡ እንደሚታወቀው የዶክተር መረራ አብረን እንስራ እስከ “ግንባር” ብቻ ነው፡፡
የዶክተር መረራ የቡዳ ፖለቲካ ብሂል በሁሉም ጉዳይ ችግሮችን ወደሌሎች ማላከክ ባለብን አባዜ ጥሩ ገላጭ ቢሆንም፤ የዚህ የቡዳ ፖለቲካ ሰለባ ዋነኛው ግን ዶክተር መረራ መሆኑ ብዙ ማሳያ ማቅረብ ይቻላል፡፡ በተለይ መድረክ የሚባለውን ስብስብ አንዴም እንኳን ለሚፈጠሩት ችግሮች ኃለፊነት የሚወሰድ አካል አድርጎ አያቀርበውም፡፡ ዶክተር መረራ በሚመራው ድርጅት ውስጥም ያለውን ችግር ለማየት እና ለማስተካከል አይፈልግም፡፡
የዶክተር መረራ “የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ሕልሞቸ” የሚለው መፅኃፍ ይህች ሀገር ከፈታና የምትወጣው እና ህልሞች ቅዠት ሳይሆኑ አውን የሚሆኑት “የኦሮሞ ልኢቃን” እና “የአማራ ልሂቃን” የያዙትን ፅንፍ ሲተዉ እና መሃል መንገድ ላይ ሲገናኙ እንደሆነ ይገልፃል፡፡ እኔ በፍፁም ያልገባኝ “የአማራ ልሂቅን” የሚባለው ፍረጃ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊ ብሄረተኝነት የሚያቀነቅኑት ለማለት ከሆነ ሌሎችም አማራ ያልሆኑ በዚህ ረድፍ ውስጥ ይገኛሉ፡፡ ወይም ደግሞ አማራ ማለት ኦሮሞ ያልሆነ ሁሉ ማለት እንደሆነ በግልፅ ሊነግረን ይገባ ነበር፡፡ ወጣም ወረደ እኔ በመሪነት ሁሉ የተሳተፍኩበትን አንድነት ፓርቲን በአማራ ልሂቀን የሚመራ ተብሎ ተፈርጇል፡፡ ስለዚህ ይህ መሰረታዊ ስህተት ሀገራችን ከፈተና እንድትወጣ የታዘዘላት የዶክተር መረራ መድሃኒት እንደማይሰራ የሚያመላክት ነው፡፡
ዶክተር መረራ የቡዳ ፖለቲካው ሰለባ መሆኑን በደንብ የሚያሳየው “ለአንድነት ሆዴ መቁረጥ የጀመረው፤ በ2205 ክረምት የድጋፍ ማሰባሰቢያ ስብሰባዎችን በአሜሪካ ለማካሄድ ተሰማምተን ከሄድን በኋላ እነ ግርማ ሠይፉ ሙሉ በሙሉ ባልገባኝ ምክንያት የጋራ እንቅስቃሴ እንዳናደርግ ባደረጉ ጊዜ ነበር፡፡ በጊዜው ለአንድነት መሪ ለነበረው ለዶ/ር ነጋሶም ምሬቴን ገልጨ ነበር፡፡ ምሬቴ ለዶ/ር ነጋሶም የገባው ይመስለኛል፡፡ ለማረም ግን አልቻለም፡፡….”  የሚል ክስ በገፅ 147 ላይ አስፍሮዋል፡፡ ተመሳሳይ ክስ በሌለሁበት በመድረክ ስብሰባ ላይ ሰሜን ጠርቶ እንዳቀረበ ሰምቻለሁ፡፡
በመጀመሪያ ደረጃ የድጋፍ ማሰባሰቢያ ስብሰባዎችን በአሜሪካ ለማካሄድ ተሰማምተን የሚለው አውነት አይደለም፡፡ እኔም እርሱም በግላችን አሜሪካ እንደምንሄድ ሲታወቅ ከተቻለ በጋራ ስብሰባ ብናደርግ የሚል ሃሳብ አንሰተን ሙከራ እንድናደርግ በሚል “አዲስ ቪው ሆቴል” ተገናኝተን ተነጋግረናል፡፡ ሙከራ ደግሞ ሊሳካም ላይሳከም ይቸላል፡፡ ይህን ዶክተር ነጋሶ ለአንድነት ድጋፍ ሰጪዎች ገልፀውላቸዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ዶክተረ መረራ ዘወትር እንደሚያደርገው “የኦሮሞ ኮሚኒቲ” ለብቻው ሰብሰቦ ገንዘብ ያሰባሰብ ነበር፡፡ ይህ ገንዘብ ለመድረክ የሚገባ አይደለም፡፡ ከዚህ በሚተርፈው ጊዜ የአንድነት ድጋፍ ሰጪዎች ስብሰባ እንዲጠሩ ጥያቄ ቀረበላቸው፡፡ የአንድነት ድጋፍ ሲጪዎች በጣም በሰለጠነ ሁኔታ ስብሰባ አድርገው በቂ ዝግጅት ሳይደረግ ድንገት የዚህ ዓይነት ስብሰባ መጥራት እንደሚቸገሩ አስታወቁ፡፡ በወቅቱ ደግሞ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል አንድነት ለጀመረው ዘመቻ ድጋፍ እያሰባሰቡ ስለሆነ ተጨማሪ ሌላ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ለማድረግ ጊዜ እንደሚወስድባቸው ምክንያታቸውን ገለፁ፡፡ ይህን ለዶክተር ነጋሶም፣ለዶክተር መረራም ተነግሯል፡፡ ዶክተር መረራ ግልፅ ሆኖ ያልገባው ምን እንደሆነ አልገባኝም፡፡ የኦሮሞ ኮሚኒቲን ሰብሰቦ ለድርጅቱ ገቢ እየሰበሰበ፣ የአንድነትን ለመድረክ አድርጉት የሚለውን ዝግጅት ያልተደረገበትን ጥያቄ አንቀበልም ማለት ለምን እንዳሰከፋው አላውቅም፡፡ በግሌ ለመድረክ ገቢ ለመሰብሰብ ዝግጁ መሆኔን በተደጋጋሚ ገልጨለት እያለሁ ግን ለምን ሊከሰኝ እንደፈለገ አላውቅም፡፡
ሌላው ዶክተር መረራ በመድረክ ውስጥ አነድነትን የአማራ ወኪል ለማድረግ የሚሰራውን ሸፍጥ (ኦፌኮ በኦሮሚያ፤ አረና በትግራይ፤ የፕ/ሮ በየነ ድርጅቶች በደቡብ) መታገል ሳይችል “አንድነት ከመድረክ ካልወጣሁ” ብሎዋል በሚል ይከሰናል፡፡ ይህን ሸፍጥ ግልፅ የሚያደርገው መድረክ በ2007 ምርጫ አንድም ዕጩ በአማራ ክልል ያለማቅረቡ ነው፡፡ እውነቱ አንድነት እንደ ፓርቲ ከመድረክ የመውጣት ጥያቄ አንስቶ አያውቅም፤ በግለሰብ ደረጃ የመውጠት ፍላጎት ያላቻው የሉም ማለት አይቻልም፡፡ አሁን ከመድረክ ጋር ለመስራት ሽር ጉድ የሚለው ሰማያዊ ፓርቲ መስራቾች ከአንድነት የወጡበት ምክንያቱ አንዱ የመድረክ ጉዳይ ነበር፡፡ አንድነት የነበረው ጥያቄ መድረክ የእውነት “ግንባር” ወይም “ውህድ” ፓርቲ ይሁን ነበር ጥያቄው፡፡ በግልፅ ዶክተር መረራ የውህደት ተቃዋሚ ሲሆን ሁሉም የመድረክ አባል ድርጅቶች አንድነት ላይ ያላቸው የጋራ ጥያቄ የገንዘብ ምንጫችን ይዋሃድ የሚል ነበር፡፡ በመጨረሻም አንድነት “በሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በጀመረው ህዝባዊ እንቅስቃሴ ከኢህአዴግ እኩል የተረበሹት የመድረክ አመራሮች አንድነትን ከመድረክ አግደው፣ እንደ ኢህአዴግ ይቅርታ ካልጠየቀ አይገባም ሲሉ የአንድነት አባላት ደግሞ መድረክ ሲታዘል ተንጠልጥሎ የቀረ ሰለሆነ ከጫንቃችን ይውረድ ብለው ወስነዋል፡፡ ይህ ደግሞ ተገቢ ውሳኔ ነበር፡፡
አንድነት ከመድረክ መልቀቅ ብዙም ሳይወራ አንድነት በሁለት ሺ ሰባት ምርጫ ላይ በያዘው ግልፅ አቋም መነሻ በስርዓቱ እንዲፈርስ ሲወሰን ከመድረክ ባንወጣ አንድነት ሳይፈርስ እንደሚቆይ እንረዳለን፡፡ ውሳኔያቸን ግን አሁን መድረክ እና አባል ድርጅቶቹ ባሉበት አቋም በፓርቲ ሰም ከመኖር ለጥቂት ጊዜም ቢሆን ባሳየነው ቁርጠኝነት የበለጠ እንደሰታለን፡፡ አንድነት ከመድረክ ወጥቶም በግዛቸው ሸፈራው መሪነት ቢቀጥል መንግሰት ይህን አሳፋሪ እርምጃ አይወስድም ነበር፡፡ ምክንያቱም ባለበት የሚረግጥ ፓርቲ ማንም አይፈራውም፡፡ ግብ አስቀምጠን የምንሄድበትን አውቀን ስንሄድ ነው ፈተናው የመጣው፡፡ ዶክተር መረራ እንደፃፈው አንድነት የፈረሰው ከባለራዕይ ወጣቶች፣ ከሀረና፣ ከኦፌኮ፣ ወዘተ በመጡ አምስተኛ ረድፈኞች አይደለም፡፡ ከተለያየ ፓርቲ ወጥተው በተለይ ከብሄር ፓርቲ ለቀው አንድነትን የተቀላቀሉ ወጣቶች አንድነት ዶክተር መረራ እንደሚለው የአማራ ልሂቃን ሳይሆን የሁሉም ቤት መሆኑን በመረዳታቸው ነው፡፡ ይህን መራራ እውነት ደክተር መረራ መቀበል የግድ ነው፡፡ አንድነት የሁሉም ቤት መሆኑ ያስፈራው መንግሰት ያለምንም አፍረት አንድነትን ለማፍረስ የተነሳውም በተለይ በኦሮሚያ ስናደርገው የነበረው ያልተጠበቀ ንቅናቄ ጭምር ነው፡፡ አንድትን ለማፍረስ የተሰለፉት ሆዳሞች ደግሞ ከሁሉም ሰፈር የተሰበሰቡ ናቸው፡፡ ይህ ደግሞ የድርጅት ስራችን ክፍተት መሆኑን እናምናለን፡፡
በመጨረሻ ዶክተር መረራ የአምቦ ወጣቶች እሰኪነግሩት ተሸፍኖበት የነበረው አውነት “የከብት ሌባን የሚጠብቀው ባለቤቱ ነው፤የኮሮጆ ሌባን የሚጠብቀው ህዝብ ነው፡፡” የሚለው ነው፡፡ አንድነት ፓርቲ በ2007 ምርጫ እሳተፋለሁ ሲል በአደባባይ የተናገርነው “ምርጫ ቦርድን ቁጥር ደማሪ እናደርገዋለን” የሚል ነበር፡፡ አንድም ምርጫ ጣቢያ ላይ ድምፁን የሚጠብቅ ህዝብ ካለሰለፍን ብንሰረቅም አንጮህም ብለን ተነሰተን ነበር፡፡ አሁንም ዶክተር መረራ ዘግይቶም ቢሆን እንደተረዳው የኮሮጆ ሌባን ለመጠበቅ የሚቆም መረጫ በሌለበት ምርጫ ፌዝ ነው፡፡ ለመምረጥ የተመዘገበ፤ ለሚደግፈው ድምፅ የሚሰጥ፣ የሰጠውን ድምፅ በትክክል የሚቆጥር ህዝብ ሲኖር ምርጫ ወደዲሚክራሲ መሸጋገሪያ ይሆናል፡፡ ይህ እንዳይሆን የሚከለክል መንግሰት ደግሞ በሌላ መንገድ ወንበሩን ለመልቀቅ መረጧል ማለት ነው፡፡
ቸር ይግጠመን!!!

Tuesday, January 12, 2016

በውጥረት ላይ ውጥረት መደራረብ ይቁም (አፈንዲ ሙተቂ)



ሰሞኑን በኦሮሚያ እና በሰሜን ጎንደር የተከሰተው የተቃውሞ ንቅናቄ ሀገሪቱን ውጥረት ውስጥ ከትቷታል፡፡ አመጹ እየተጋጋለ መሄድ እንጂ የመቀዛቀዝ ባህሪ አላሳይ ብሏል፡፡ አሁንም በልዩ ልዩ አካባቢዎች ቀጥሏል፡፡ በአራቱም አቅጣጫዎች ውጥረት ሰፍኗል፡፡ በህይወት ዘመኔ ይህንን ያህል ዘላቂ ሆኖ የቆየ አመጽ አይቼ አላውቅም፡፡ በዚህ አመጽ ለጠፋው ህይወትና ንብረት እናዝናለን፡፡ በየትኛውም ወገን ሆኖ በትርኢቱ ውስጥ የተሳተፈው የኛው ዜጋ በመሆኑ ነፍሱና አካሉ ታሳዝነናለች፡፡ ታዲያ አመጹ የተከተሰው በመንግሥት ሚዲያ እንደሚነገረው “ኪራይ ሰብሳቢዎች፣ ግንቦት ሰባቶችና ኦነጎች በወጠኑት ሴራ ነው” የሚለው ምክንያት መሰረት የለውም፡፡ እንደዚህ ማለት “ህዝቡ አያገናዝብም፤ በማንም ይታለላል” የማለትን ያህል ነው፡፡ በኤርትራ የመሸጉት ድርጅቶችም ሆኑ “ኪራይ ሰብሳቢ” የሚባሉት የማይታወቁ ሃይሎች በዚህ አመጽ ላይ የተለየ ሚና የላቸውም፡፡ ድርጅቶቹ አመጹን ደግፈው መግለጫ መስጠታቸው የአመጹ ቀስቃሽም ሆነ መሪ ሃይል የሚያስብላቸው አይደለም፡፡ አመጹ የተወለደው የህዝብ ብሶቶች እንደ ኩሬ ውሃ እየተጠራቀሙ ከግድባቸው አልፈው መፍሰስ በመጀመራቸው ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ለነዚህ የህዝብ ብሶቶች ተጨባጭና ወቅታዊ ምላሽ እየሰጠ ኩሬውን ማድረቅ ነበረበት፡፡ ነገር ግን ከህዝብ ከሚነሳው ቅሬታ ይልቅ ካድሬዎቹ በሚጽፉት አማላይ ሪፖርት ስለሚታለል ስለብሶቶቹ የሚያወሳውን ሁሉ እንደ ተቃዋሚ ያይ ነበር፡፡ ትክክለኛ ተቃዋሚዎችን ደግሞ በአቋራጭ ስልጣን ለመያዝ የቋመጡ ተስፈኞችና ሁከት ፈጣሪዎች ብሎ ከመፈረጅ ውጪ እንደ ተቃዋሚ የማየት ችግር አለበት፡፡ ተቃዋሚዎች ከሚያነሱት የተቃውሞ ሃሳብ መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆነው በተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሰረተ መሆኑን አይገነዘብም፡፡ የነዚህ ሁሉ ግድፈቶች ድምር ነው እንግዲህ ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት እያሰለሱ ሲፈነዱ የነበሩትን አመጾች ሲቀሰቅሱ የነበሩት፡፡ የኢፌዴሪ መንግሥት አሁን አመጹን (በርሱ አገላለጽ “ሁከቱ”ን) ተቆጣጥሬአለሁ እያለ ነው፡፡ ነገር ግን ከሁኔታው ትምህርት ቀስሞ ለህዝብ ጥያቄዎች ተጨባጭ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ አሁንም ተመሳሳይ ስህተት ወደ መስራቱ ነው ያዘነበለው፡፡ ለምሳሌ በብዙ የኦሮሚያ እና የአማራ ክልል አካባቢዎች ሰዎች በገፍ እየታሰሩ ነው፡፡ ባለፈው ሳምንትም ሁለት የኦፌኮ አመራር አባላት እና የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ታስረዋል (አንደኛው በቅርቡ የተለቀቁት አቶ በቀለ ገርባ ናቸው)፡፡ አንዳንድ ሰዎችም ከስራ ገበታቸው እየተወገዱ ስለመሆናቸውም እየተነገረ ነው፡፡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና መምህራንም ከትምህርታቸውና ከስራቸው መባረራቸውና መታሰራቸው ተዘግቧል፡፡ ይህ ሁሉ ባለፉት ሃያ አራት ዓመታት ሲደረግ ነበር፡፡ ነገር ግን ህዝቡ ይህንን ፈርቶ ለተቃውሞ እና ለአመጽ ከመውጣት አልታቀበም፡፡ ብሶቱ ሲያንገሸገሽው ለተቃውሞ ይወጣል፡፡ መንግሥት ለወደፊቱ ተመሳሳይ አመጽ እንዳይከሰት ከፈለገ የህዝቡን የልብ ትርታ ነው ማዳመጥ ያለበት፡፡ ዘወትር የሚወቀስበትን ተቃውሞን በጸጥታ ሃይል የመቆጣጠር ስልትን ተከትሎ በውጥረት ላይ ውጥረት መጨመር አይገባውም፡፡ —- መንግሥት ራሱን አንቅቶ ሀገሪቱን መምራት የሚሻ ከሆነ በሶስት ደረጃዎች የሚተገበሩ እርምጃዎችን መውሰድ ያለበት ይመስለኛል፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ከሚፈጸሙት ተግባራት መካከል የመጀመሪያው በቅርቡ የተካሄደው ንቅናቄ “የህዝብ አመጽ” መሆኑን ማመን እና ይህንኑ በየደረጃው ላሉት አባላትና ደጋፊዎቹ የማሳመን ስራ ነው፡፡ በምዕራብ ኦሮሚያ ጫፍ ከምትገኘው መንዲ ጀምሮ እስከ ምስራቅ ሀረርጌዋ የኮምቦልቻ ከተማ የሚኖረው ህዝብ የተሳተፈበትን ተቃውሞ “የጥቂት ነውጠኞች” ተቃውሞ እያሉ ማጥላላት አይቻልም፡፡ ንቅናቄው የኢህአዴግ መሪዎች በአድናቆት ከሚያወድሷቸው የራያ (ቀዳማይ ወያነ)፣ የጎጃም እና የባሌ ገበሬዎች አመጽ ጋር እንጂ አይተናነስም፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት እንደሚለው ንቅናቄው የተለኮሰው “ሽብርተኞች፣ ኒዮ-ሊበራሎች፣ ጋኔሎች እና ጋንግስተሮች” ባደረጉት ቅስቀሳም አይደለም፡፡ ስለዚህ ተቃውሞው የህዝብ እንደሆነ ማመን ይገባል፡፡ ከመንግሥት የሚጠበቀው ሁለተኛው ተግባር ደግሞ ተቃውሞው የህገ-መንግሥት ይከበር ጥያቄ መሆኑን ማመንና ማሳመን ነው፡፡ ለምሳሌ በአዲስ አበባው ማስተር ፕላን ጉዳይ ላይ የቀረበው ጥያቄ የህገ-መንግሥት ይከበር ጥያቄ ነው፡፡ ህገ-መንግሥቱ “የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ላይ ልዩ መብት አለው” በማለት ደንግጎ ሳለ ከዚህ ድንጋጌ ጋር በቀጥታ የሚጋጭ ማስተር ፕላን መንደፍ ምን ማለት ነው…? አዲስ አበባ ለኦሮሚያ መስጠት የሚገባውን ልዩ ጥቅም ሳይሰጥ ሃያ ዘጠኝ የኦሮሚያ ከተሞችንና ከሚሊዮን የበለጠ ደሃ ገበሬ የሚኖርበትን መሬት ደረጃ በደረጃ በአዲስ አበባ ውስጥ ለማካለል መሞከር በየትኛው የህገ-መንግሥቱ አንቀጽ ነው የሚፈቀደው? በዚያ ላይ ማስተር ፕላኑ ከሁለት ዓመታት በፊት ደም ያፋሰሰ መሆኑ እየታወቀ እና ለወደፊቱ ይቀራል ተብሎ ለህዝቡ ተነግሮ ሳለ ዘንድሮ ላይ ለተፈጻሚነቱ መንቀሳቀስ ጥቅሙ ለማን ነው….?. ህዝቡ ከህግ አግባብ አልወጣም፡፡ የየማስተር ፕላኑን ጥያቄ ጨምሮ ህዝቡ የተንቀሳቀሰላቸው ሌሎች ታላላቅ ጥያቄዎች ሁሉ ህገ-መንግሥቱን የማስከበር ጥያቄ እንደሆነ ማመንና ለተፈጻሚነታቸው መንቀሳቀስ ተገቢ ይመስለኛል፡፡ ሶስተኛው ታላቅ ተግባር ደግሞ በመንግሥት የሚሰነዘሩ ሃሳቦችንም ሆነ ፖሊሲዎችን የማይቀበለውን ዜጋና ድርጅት እንደ ሀገር ጠላት አድርጎ የሚፈርጀውን ኮሚኒስታዊ እሳቤ ማቆም ነው፡፡ በተግባር እንደሚታወቀው ኮሚኒስቶች እነርሱን የሚቃወመውን ሁሉ እንደጠላት ነበር የሚፈርጁት፡፡ ይህ ኮሚኒስታዊ አረዳድ በሀገራችን ውስጥ ምን አይነት ጥፋት እንዳስከተለ እናውቃለን፡፡ ለቀይ ሽብር መከሰት ዋነኛው ምክንያት የነበረው በ1966 ዓብዮት ማግስት ባበቡት ድርጅቶች መካከል የነበረው የአቋም ልዩነት ሳይሆን ድርጅቶቹ ከነርሱ የተለየ ርዕዮት ያለውን ዜጋና ቡድን በጅምላ እንደ ጠላት የሚያዩበት ኮሚኒስታዊ (ግራ-ዘመም) ዘይቤአቸው ነው፡፡ ኢህአዴግም የኮሚኒዝም አቀንቃኝ በነበረበት ዘመን ከርሱ የሚለዩትን ሁሉ በጠላትነት ይፈርጅ ነበር፡፡ ታዲያ ዛሬ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ተከታይ ነኝ በሚልበት ዘመን እንኳ ከዚያ የጥንት ልማዱ ሙሉ በሙሉ አልተላቀቀም፡፡ ይህ ልማድ ካልቀረ ደግሞ ለሀገር በትክክል የሚያስበውን ዜጋ ለይቶ ማወቅ አይቻልም፡፡ ለሀገር ተቆርቁሮ በመንግሥት ፖሊሲዎችና የልማት ፕሮግራሞች ላይ ትችት የሚሰነዝረው በሙሉ እንደ ጠላት ስለሚፈረጅ የርሱ ሃሳብ አይደመጥም፡፡ የሚገርመው ደግሞ መንግሥት ብዙ ከተጓዘ በኋላ ከነዚህ ተቆርቋሪ ዜጎች የተሰነዘሩትን ሃሳቦች አምኖ የሚቀበል መሆኑ ነው፡፡ ምሳሌ ልስጣችሁ፡፡ በ1994/95 ሀገራችን ልክ እንደ አሁኑ በከፍተኛ ድርቅ ተመትታ ነበር፡፡ በዚያ ዘመን የገበሬውን ህይወት ለመለወጥ በሚል መንግሥት በተግባር ላይ ካዋላቸው ፕሮግራሞች መካከል አንዱ “ውሃ ማቆር” የሚባለው ነው፡፡ ሃሳቡ በአጭሩ “ገበሬው በክረምትና በበልግ ወራት የሚዘንበውን ዝናብ በጉድጓድ አጠራቅሞ ዝናብ በጠፋበት ወቅት ይጠቀምበት” የሚል ነው፡፡ ይሁንና የተለያዩ የውሃ ኤክስፐርቶች ይህ አሰራር ሀገር አጥፊ መሆኑን ማስረጃ እየጠቀሱ ሞገቱ፡፡ ለምሳሌ “በኩሬ የተጠራቀመው ውሃ ቀስ በቀስ ወደ መሬት እየሰረጎደ ስለሚገባ የገበሬው ልፋት ከንቱ ሆኖ ይቀራል፤ በተጨማሪም በጉድጓዱ ውስጥ ደለል ስለሚገባበት ገበሬው የሚፈልገውን ያህል ውሃ ማጠራቀም አይቻልም” ተብሎ ነበር፡፡ በሌላ በኩል ውሃው ለወባ መራቢያ አመቺ በመሆኑ በገበሬው ጤና ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል” የሚል ስጋት ከውሃ እና ከጤና ኤክስፐርቶች ተነግሯል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ለነዚህ ሃሳቦች ዋጋ በመስጠት ፈንታ “ጠላቶቻችን ልማታችንን ለማደናቀፍ የሰነዘሩት ሃሳብ ነው” እያለ ማጥላላትን ነው የመረጠው፡፡ ይሁንና በሂደት ሁሉም ችግሮች ቀስ በቀስ እየታዩ መከሰት ጀመሩ፡፡ ውሃው ወደ ኩሬ ውስጥ ከገባ በኋላ በኩሬው ውስጥ ከመቆየት ይልቅ ወደ መሬት ውስጥ እየሰረጎደ እንደሚገባ ታወቀ፡፡ መንግሥት ይህንን ለማስቀረት በሚል በኩሬው ውስጥ ፕላስቲክ ይነጠፍ ማለት ጀመረ፡፡ ከአንድ ዓመት በኋላ ግን ታላቅ አደጋ ተከሰተ! በዚያ የውሃ ማቆር ዘመቻ ሳቢያ ሀገሪቱ በታሪክ ያላየችው የወባ በሽታ ተጠቂ ሆነች!! መንግሥቱ በድርቅና በወባ ተወጠረ፡፡ አንደኛውን ችግር በአስቸኳይ ማስወገድ ስለነበረበት እንደዚያ የተለፋበትና የፕሮፓጋንዳ ጥሩምባ የተነፋለት የውሃ ማቆር ዘመቻ በ1997 አጋማሽ ላይ ለማንም ሳይነገር ተሰረዘ፡፡ ከዚያ በኋላ ስለርሱ ያወራ የለም፡፡ በቃ “የውሾን ነገር ያነሳ ውሾ” ሆኖ ቀረ!!! የኢትዮጵያ መንግሥት ከያኔው ስህተቱ ተምሮ ከምሁራን የሚሰነዘሩ ሃሳቦችን መስማት ነበረበት፡፡ ነገር ግን አሁንም ከአስራ ሁለት ዓመታት በኋላ ጆሮውን ለምሁራን ውትወታ ሲከፍት አይታይም፡፡ በዚህ አያያዝ መቀጠል የህዝብ ብሶትን ማጠራቀም ነው የሚሆነው፡፡ ስለዚህ ሃሳብ የሰነዘረን ግለሰብ እና ቡድን አክብሮ ለሃሳቡ ዋጋ መስጠትና መመርመር፣ እንደዚሁም ሃሳቦቹን ጠቅልሎ ከመዘነ በኋላ ለተግባራዊነታቸው መንቀሳቀስ ይገባል፡፡ —– በሁለተኛው ደረጃ ላይ የሚከናወኑት ተግባራት ከህዝቡ ህይወት ጋር በቀጥታ ለሚገናኙ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡባቸው ናቸው፡፡ ለምሳሌ ገበሬው ብሶት የሚያሰማበትን በግዴታ ላይ የተመሰረተ ማዳበሪያ የመጠቀም አሰራር እና ከተሜው ለሚማረርባቸው የኑሮ ውድነትና ስራ አጥነት አፋጣኝ መፍትሄዎችን መሻትን ይጨምራል፡፡ ሁሉም ዜጋ የሚንገሸገሽባቸው የመልካም አስተዳደር እጦትና የሙስና አሰራርም የመንግሥትን ፈጣን እርምጃ ይሻሉ፡፡ ከመደበኛ ነጋዴዎች የተለየ ድጋፍ የሚደረግላቸው ኢንዶውመንት ፈንድስ የሚባሉት ድርጅቶች (ኤፈርት፣ ጥረት፣ አምባሰል፣ ዲንሾ፣ ቱምሳ፣) ትክክለኛውን ህጋዊ መስመር ይዘው እንዲሰሩ መደረግ አለባቸው፡፡ ብዙዎች “የጆሮ ጠቢ ስርዓት” እያሉ የአንድ ለአምስት አደረጃጀትን ማስወገድና የወጣቶችና የሴቶች ሊግ አባላት ብቻ እየተመረጡ ተጠቃሚ የሚሆኑበት የጥቃቅንና አነስተኛ ስራ ፈጠራ ፕሮጀክት ለብዙሃኑ ህዝብ ክፍት ማድረግ ይገባል ፡፡ በዚህ ረገድ የሚሰሙት ብሶቶች ከህዝቡ ህይወት ጋር በቀጥታ የተገናኙ በመሆናቸው ሌላ የህዝብ ቁጣ እንዲነሳ የማድረግ አቅማቸው ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ ብሶቶቹን በጊዜ ለመቅረፍ መንቀሳቀስ ይገባል፡፡ በሶስተኛ ደረጃ የሚፈጸሙት ስትራቴጂያዊ እቅድ ወጥቶላቸው የሚተገበሩ ስራዎች ናቸው፡፡ ከነዚህም መካከል አንዱ አዲስ የከተሞች ልማት ስትራቴጂ መቅረጽ ነው፡፡ የኢህአዴግ መንግሥት እስከ አሁን ድረስ የሚሰራበት የከተሞች ልማት ስትራቴጂ አዲስ አበባን ወደ ጎን ከመለጠጥ እና አስከፊውን የመሬት ቅርምት ዘመቻ ከማባባስ ውጪ በከተሞቻችን እድገት ላይ ያመጣው ተጨባጭ ለውጥ አነስተኛ ነው፡፡ በአንዳንድ ከተሞች የተወሰኑ ፎቆችንና መለስተኛ ፋብሪካዎችን ለማየት ቢቻልም በከተሞቻችን መካከል ተመጣጣኝ እድገት ማምጣት አልተቻለውም፡፡ የመንግሥቱ ትኩረት በአዲስ አበባ ላይ ብቻ በመሆኑ የክልል ከተሞች ከእንፉቅቅ ጉዞ ሊወጡ አልቻሉም፡፡ አዲስ አበባ እየተለጠጠች በማስተር ፕላን ስም የኦሮሚያ መሬቶችን ለመዋጥ ያሰፈሰፈችው የፌዴራል መንግሥቱ ለከተማዋ የሰጠው ገደብ የለሽ አትኩሮት በርካታ ፍላጎቶችን ስለቀሰቀሰ ነው፡፡ ስለዚህ እንዲህ ዓይነቱ ወልጋዳ የከተሞች እድገት ስትራቴጂ ተወግዶ ሁሉም ከተሞቻችን ተጠቃሚ የሚሆኑበትን አዲስ የከተማ ልማት ስትራቴጂ መቀረጽ ይኖርበታል፡፡ ሌላው ደግሞ ዲሞክራሲን በትክክል የማስፈን ስራ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ቢታወጅም ሀገሪቱ በተጨባጭ የምትመራበት ስርዓት ስያሜ በየትኛውም መዝገበ-ቃላት ተፈልጎ የሚገኝ አይመስለኝም፡፡ ህገ መንግሥቱ ከአንዳንድ አንቀጾቹ በስተቀር በምዕራቡ ዓለም ያሉትን ህገ-መንግሥቶች ይመስላል (አብዛኛው ክፍሉ ከፈረንሳይ ህገ-መንግሥት የተገለበጠ ነው ይባላል)፡፡ በመሆኑም “ተራማጅ” ሊባል የሚችል ጤናማ ህገ-መንግሥት ነው፡፡ በአንዳንድ አንቀጾቹ ላይ (አንቀጽ 39፤ የመሬት አዋጅ ወዘተ…) የሚሰነዘሩት ጥያቄዎች ሀገሪቷ ወደ እውነተኛ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ኑሮ እድገት ውስጥ በምትገባበት ጊዜ በሚፈጠረው ብሄራዊ መግባባት ሊመለሱ ይችላሉ፡፡ ችግሩ ግን ኢህአዴግ እንዲህ ዓይነቱን ተራማጅ ህገ-መንግሥት አጽድቆ ለርሱ ተገቢውን አትኩሮት የማይሰጥ መሆኑ ነው፡፡ ድርጅቱ ከህገ-መንግሥቱ ይልቅ በፓርቲ ደረጃ ለሚመራባቸውና ለሚያምንባቸው መርሖዎች ከፍተኛ ስፍራ ይሰጣል፡፡ እነዚህ መርሖዎች በአብዛኛው ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የተገለበጡ ነው የሚመስሉት፡፡ እነዚህ የፓርቲው መርሖዎችና ህገ-መንግሥቱ ሰማይና መሬት ናቸው፡፡ ሁለቱ ባልተጣጣሙበት ሁኔታ ትክክለኛ ዲሞክራሲን ማስፈን አይቻልም፡፡ ስለዚህ ፓርቲው መርሖዎቹን እንደገና በህገ-መንግሥቱ አቅጣጫ አስተካክሎ ራሱን ለፉክክር ማዘጋጀትና ሀገሪቱ ከጭምብል ዲሞክራሲ ወደ እውነተኛ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት የምትሸጋገርበትን ስርዓት ለመገንባት ሌት ከቀን መጣር አለበት፡፡ —— ከላይ በግሌ የሰነዘርኳቸው የመፍትሔ ሃሳቦች ሙሉእ አይደሉም፡፡ የህዝብን ብሶት ለማሻርና እምባውን ለማበስ የሚሰሩት ስራዎች በጣም በርካታ ናቸው፡፡ እኔ እነኝህን የመፍትሄ ሃሳቦች የጠቀስኳቸው ችግሮችን ዘርዝሬ መፍትሔዎችን ካልጠቆምኩ “ችግር ዘምዛሚ” የሚል ስም እንዳይሰጠኝ በመፍራቴ ብቻ ነው፡፡ ይሁንና መንግሥት መፍትሔ ሰጪ መሆንን የሚሻ ከሆነ እኔ የጻፍኩትን ባይሆን እንኳ ጉዳዩን ይበልጥ መዘርዘር ከሚችሉ ምሁራንና ተቋማት የሚሰነዘሩትን የምክር ሃሳቦች ይስማ እላለሁ፡፡ በልዩ ልዩ ከተሞች አመጹን ለማስቆም በሚል በጸጥታ ሃይሎች የሚካሄደው ግድያ፣ እስራትና ከስራ መፈናቀል በውጥረት ላይ ውጥረትን እየደራረበ ሀገሪቷን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ ከመውሰድ ውጪ ወደ መፍትሔ አያመሩንም፡፡ ስለዚህ እነርሱን በአስቸኳይ ማቆምና ለህዝብ ጥያቄዎች መፍትሔ የመሻት ስራዎች ላይ መረባረብ ይገባል፡፡ “ህዝቡ መቶ ፐርሰንት መርጦኛል” የሚለው የኢትዮጵያ መንግሥት በእውነትም ለህዝብ ጥቅም የቆመ ህዝባዊ መንግሥት ከሆነ ጆሮውን ከፍቶ ህዝቡን ማዳመጥ አለበት፡፡ —– አፈንዲ ሙተቂ

Sunday, January 3, 2016

የመጨረሻዉ መጀመሪያ — አሜሪካ ለምን የአርባ ምንጭ የሰዉ አልባ አይሮፕላን ማስነሻ ጣቢያዋን መተዉ አስፈለጋት? (ከሳዲቅ አህመድ)

ወደ አለም አቀፉ የዲፕሎማሲ መንደር ቀረብ ቀረብ ማለት ከጀመሩ ወራት ተቆጥረዋል። ከሐያላኑ አገራት ጋር የቀጥታ ሳይሆን የእጅ አዙር የዲፕሎማሲ ጉዞን ሳይጀምሩ አልቀሩም የሚሉም አሉ። በጠመዝማዛዉ መንገድ የሚጓዙት የዲፕሎማሲ ጉዞ ከሚፈልጉበት ቦታ እስኪያደርሳቸዉ ድረስ እምብዛም አትኩሮት አልሳቡም። እርሳቸዉ ግን እየተጓዙ ነዉ። ፕሬዝዳንት ኢሳያስ  አፈርቂ።

ዜናዉ፦

አሜሪካ አርባ ምንጭ ዉስጥ ያላትን የሰዉ አልባ አይሮፕላን ማብረሪያ ጣብያ መጠቀም ማቆሟ ታወቀ

በሱማሊያ ያሉትን አል-ሸባቦች ለማጥቃት አሜሪካ እንደ ኢሮጵያዉያን አቆጣጠር ከ2011 ጀምሮ ትጠቀምበት የነበረዉን የሰዉ አልባ አይሮፕላን ማስነሻ ጣብያ መጠቀም ማቆሟን አሶሽየትድ ፕሬስ አዲስ አበባ ያለዉን የአሜሪካ ኤምባሲ ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
ዴቪድ ኬኔዲ የተባሉት የኤምባሲዉ ቃል-አቀባይ ለአሶሽየትድ ፕሬስ በኢሜይል በላኩት መልእክት ሁለቱ አገራት ባደረጉት ስምምነት አሜሪካ በአርባ ምንጭ የምታደርገዉ ቆይታ አስፈላጊ አይደለም።የኤምባሲዉ ቃል አቀባይ ይህንን ቢሉም የኢትዮጵያና የአሜሪካን ግንኙነት የሚከታተሉ ባለሙያዎች ክስተቱ አሜሪካ የፖሊሲ ለዉጥ ማረግ መጀመሯን አመላካች ዱካ ሊሆን ይችላል ሲሉ ይጠቁማሉ።
ለጋሽ አገራትና ፍላጎታቸዉ
የቀድሞዉ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆርጅ ቡሽ ሽብር ፈጠራን የመዋጋት ዘመቻ ማወጃቸዉ የሚዘነጋ አይደለም።ኢትዮጵያ የዚሁ ሽብር ፈጠራን የመከላከል ሚና ተሰጥቷትበምላሹ ከለጋሽ አገራት ድጎማን ስትቀበል መቆየቷ ይታወቃል።መረጃዎች እንደሚያመላክቱት አሜሪካ ለኢትዮጵያን በደንብ አርጋ ትለግሳለች። በ2008እንደ አዉሮፕያዉያኑ አቆጣጠር አሜሪካ ለኢትዮጵያ 969ሚሊዮን ዶላር ለግሳለች። በ2009 916 ሚሊዮን ዶላር፣በ2010 የለገሰችዉ ወደ 513 ሚሊዮን ዝቅ ማለቱ ይታወቃል።
አሜሪካ ኢትዮጵያን የምትለግሰው አገሪቷ ዉስጥ የሚከሰተዉን የድርቅና የርሃብ አደጋ ለመከላከል፣ድህነትን ለመቋቋም፣ ለመልካም አስተዳደር፣ ማህበራዊ ሁናቴዎች ላይ ያሉ መመሪያዎችን ለማሻሻልና ለወታደራዊ ስልጠና መሆኑን መረጃዎች ያመላክታሉ። የሰብዓዊ መብት ተሟጋች የሆኑ ድርጅቶች ኢትዮጵያ ዉስጥ ከፍተኛ የሆነ የሰብዓዊ መብት ረገጣ በመኖሩ አሜሪካ እና ሌሎች ለጋሽ አገራት የሚለግሱት ገንዘብ የአገሪቱን ዜጎች ህልዉና አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን ያስጠነቅቃሉ።
አኩሪ ስራን ሰሪ ወይስ ሽብርን ፈጣሪ?
የአሜሪካዉ ፕሬዝዳት በራክ ኦባማ በሐምሌ 20/2007 ወደ ኢትዮጵያ በተጓዙበት ወቅት “ኢትዮጵያ ሽብር ፈጠራን በመከላከል ጽኑ የአሜሪካ አጋር ናት፣ ኢትዮጵያዉያን ጠንካራ ተዋጊዎች ናቸዉ” ማለታቸዉ ይታወሳል። ኦባማ ይህንን ቢሉም፤ የኢትዮጵያ መንግስትን የሚቀናቀኑ ቡድኖች በህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ የሚመራዉ መንግስት ‘ሽብር ፈጠራ በሱማሌ ዉስጥ እንዲስፋፋ ከአልሸባብ ጋር ግንኙነት ያደርጋል፣የሶማሊያን የጦር አበጋዞች እያስታጠቀ ሽብር ፈጠራን መነገጃ አድርጓል፣የኢትዮጵያ ወታደሮችን ሶማሊያ እየላከ ያስፈጃል ሲሉ መንግስትን ተጠያቂ ያደርጋሉ።ጄከብ ጁማ የተባሉ ኬንያዊ ቱጃር በመጋቢት 25/2007 በትዊተር ገጻቸዉ ላይ በለቀቁት መረጃ “የኢትዮጵያ መንግስት አሸባሪዉን አል-ሸባብ ያስታጥቃል።አዲስ አበባ ለአፍሪካ ቀንድ አለመረጋጋት ተጠያቂ ናት።የኬንያዉ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የአፍሪካዉ ህብረትና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ መንግስትን እንዲመረምሩ ግፊት ማድረግ አለባቸዉ!” ብለዉ ነበር። የቱጃሩ መረጃ አነጋጋሪ ሆኖ መሰንበቱ ይታወሳል።ለኢትዮጵያ መንግስት ቅርበት ያላቸዉ የመገናኛ ብዙሃን ጉዳዩን ለማስተባበል ስሯሯጡ መታየታቸዉ የሚዘነጋ አይደለም።
የእጅ አዙር ዲፕሎማሲ?
በህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ የሚመራዉ የኢትዮጵያ መንግስት ተቀናቃኝ አጎራባች አገራት ስለመጡበት ለምእራቡ አገራት የሚኖረዉ ስልታዊ አጋርነት እየቀነሰ ነዉ በማለት የሚገልጹም አሉ።የአሜሪካ ስልታዊ አጋር የሆኑ የባህረሰላጤዉ ሱኒ ሙስሊም አገራት የአሰብ ወደብን መገልገያ ለማድረግ መወሰናቸዉ አነጋጋሪ ሆኗል።
በአሜሪካ የዉጭና የዲፕሎማሲ ጉዳዮች 38 አመታትን ያገለገሉት አምባሳደር ሐርማን ኮህን በአፍሪካ ቀንድ እየተከሰተ ስላለዉ ፈጣን ለዉጥ በታህሳስ 18/2008 በግል ገጻቸዉ ላይ ጽፈዉ ነበር።…”እናንተ አቢሲኒያዉያን ሆይ!” ብለዉ የተጣሩት አምባሳደር ኮህን “እናንተ በእርስ-በርስ ግጭት ስትጣሉ…ስትጯጯሁና…ሳትነጋገሩ… የባህረ ሰላጤዉ መንግስታት ምሳቹን እየበሉባቹ ነዉ” ብለዉ አስጠንቅቀዋል። ኮህን አክለዉም የተባበሩት አረብ ኤምሬት አይሮፕላኖች ከአሰብ ያለማቋረጥ መንቀሳቀሳቸዉንና ሳዑዲ አረቢያ በአሰብ ላይ የ50 አመታት ኪራይ መዉሰዷን አመላካች ሪፖርቶች መኖራቸዉን ገልጸዋል።
የባህረ ሰላጤዉ የሱኒ ሙስሊም አገራት በየመን በኩል ያለዉን የኢራንንና የሺዓ መስፋፋት ለመከላከል ኤርትራ ላይ አትኩሮት ማድረጋቸዉ የሚታወቅ ነዉ። እነዚህ በነዳጅ ዘይት ገንዘብን ያካበቱ አገራት ከአሜሪካ ጋር ስልታዊ አጋሮች ናቸዉ። ከአሜሪካ ጋር በኢኮኖሚዉና በወታደራዊ ግንኙነት የዉዴታ ግዴታ ቁርኝት አላቸዉ። ወደ አሰብ መዘንበላቸዉና አሰብን መከራየታቸዉ ያለአሜሪካ ይሁንታ በራሳቸዉ ፍላጎት ብቻ የተደረገ ነዉ ለማለት አያስደፍርም።
ሽብር ፈጠራን ለመከላከል በሚል መርህ በሳዑድ አረቢያ የሚመራ የ34 አገራት ጥምር ጦር በታህሳስ 5/2008 ተመስርቷል። ይህ ጥምር ጦር የኪራዩን የአሰብ ወደብ አይጠቀምም ማለቱ አስቸጋሪ ነዉ። የጥምር ጦሩ አላማ ISIS እና ሌሎችን በኢስላም ስም የተነሱ አሸባሪዎችን ማመናመን መሆኑ እየተነገረ ነዉ።የአገራቱ ጣምራ ጦር የተዋቀረዉ ለፕሮፓጋንዳ ካልሆነና አላማዉ ተግባር ላይ ከዋለ፤ ISIS ብቻ ሳይሆን በሶማሊያ ያለዉም አል-ሸባብ የጣምራ ጦሩ ተጠቂ የሚሆንበት እድል የሰፋ ነዉ።ስለዚህ አሜሪካ ለምን አርባ ምንጭ ላይ የሰዉ አልባ አይሮፕላን ማስነሻ ይኖራታል? ስልታዊ አጋሬ የምትላቸዉን አገራትን በጅ አዙር ከመጠቀም ምን ይከለክላታል? ለምን የጠገበዉን አሳማ (ህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ) ትቀልባለች? ለአሜሪካ በጅ አዙር የተራበችዉን ኤርትራ ማብላት አይሻላትም ?
ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወቂ ለምን በአንድ አመት ሁለት ግዜ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ተጓዙ?
ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወቂ መጀመሪያ በሚያዚያ 21/2008 ወደ ሳዑዲ አረቢያ በመጓዝ ከአገሪቱ ንጉስ ሰልማንቢን አብዱል አዚዝ አል-ሱዑድ ጋር መገናኘታቸዉ በአረቡ አለም በሰፊዉ የተዘገበ ቢሆንም ኢትዮጵያዉያን እምብዛም አትኩሮት የቸሩት አይመስልም ነበር። ኢሳያስ አፈወርቂ ዳግም በታህሳስ 10/2008 ወደ ሪያድ ሳዑዲ አረቢያ የሁለት ቀን የስራ ግብኝት ለማድረግ ማቅናታቸዉ በአገራቱ መካከል የጠበቀ ስልታዊ ግንኙነት መመስረቱን አመላካች ነበር።የኢሳያስን የሳዑዲ ሁለተኛ ጉዞ ተከትሎ ኤርትራ ጣምራ የ34 ጦር አገራትን ሐይል ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንደምትደግፍ ከአገሪቱ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዉጡ መረጃዎች አመላክተዋል።
ህወሃት መራሹ የኢትዮጵያ መንግስት ለጸረ ሽብር ተግባር ከለጋሾች እርዳታ የሚቀበልበት አል-ሽባብ የጣምራ ጦሩ አባልና ደጋፊ በሆኑ አገራት ተከቧል። ሶማሊያ፣ጅቡቲ እና ኤርትራ ጣምራ ጦሩን ደጋፊ ናቸዉ።ስለዚህ አሜሪካ ለምን የሰዉ አልባ አዉሮፕላን ማስነሻዋን አርባ ምንጭ ማቆየት ያሻታል?
ማስጠንቀቅና ልመና
በጋምቤላ እና በኦሮሚያ ያሉ አርሶ አደሮችን እያፈናቀለ መሬትን ለሳዑዲ አረቢያና ለሌሎች አገራት ሲያከራይ የነበረዉ የኢትዮጵያ መንግስት አስመራም ተመሳሳይ ስራ በመጀመሯ ደስተኛ አለመሆኑን እየገለጸ ነዉ። በባለፍዉ የህዳር ወር መገባደጃ ጠቅላይ ሚኒስቴር ሐይለማሪያም ደሳለኝ ሳዑዲ አረቢያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን ማስጠንቀቃቸዉ ታዉቋል። ለአገር ዉስጥ ጋዜጣ ቃለ መጠይቅ የሰጡት ሐይለማርያም ደሰላኝ በአሰብ ወደብ ላይ የሚያደጉትን እንቅስቃሴ ተከትሎ ኢትዮጵያ ለሚኖራት ምላሽ ሐላፊነቱን ሳዑዲ አረቢያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ይሸከማሉ ብለዋል።
የጠቅላይ ሚኒስቴር ሐይለማሪያም ደሳለኝ ማስጠንቀቂያ ሳይሻር በከፍተኛ የኢትዮጵያ የመንግስት ባለስልጣናት የሚመራ የልዑካን ቡድን ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በታህሳስ23/2008 በመግባት አቡ ዳቢ ፈንድ ፎር ዴቨሎፕመንት የሚባል የተራድኦ ድርጅትዘንድ በማምራት በሁለትዮሽ የእድገት፣ የመዋእለ ንዋይ እና የእርዳታ ጉዳዮች መነጋገራቸዉ ተዘግቧል።
እየቀረበ ያለዉ ለዉጥ
ህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ በጅ አዙር አሸባሪን የመዋጋት የገበያ እሽቅድም ከጁ እየተፈተለከበት ይመስላል። ኤርትራ እና የ34 አገራት ጣምራ ጦር እየተፎካከሩት ነዉ። ስርዓቱ በከፍተኛ አጣብቂኝ ዉስጥ ገብቷል። ከዚህ አጣብቂኝ ለመዉጣትም እንደ አማራጭ የወሰደዉ የጅምላ ግድያንና እስር ነዉ። ተሰሚነት ያላቸዉ ሰዎች፣አክቲቪስቶች፣ጋዜጠኞች፣የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች፣ተማሪዎች፣ መምህራንና ሌሎችም የስ ርዓቱ ሰለባ እየሆኑ ነዉ። የማሰቃያ እና የማጎሪያ እስር ቤቶች መሙላታቸዉ እየተነገረ ነዉ። በጥቅሉ በህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ የሚመራዉ መንግስት አይደለም አሸባሪነትን ሊከላከል እራሱ አሸባሪ በመሆን ለዜጎች ህልዉና ስጋት መሆኑን የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁናቴ መቃኘቱ በቂ ነዉ።
አዲሱ የኢትዮጵያ አመት ከገባበት ግዜ ጀመሮ በተለያዩ ቦታዎች ቦምብ መፈንዳት ጀምሯል። በታላቁ አንዋር መስጊድ ዉዳሴ (መንዙማ) ሲያሰሙ በነበሩ ምእምናን ላይ በታህሳስ 1/2008 የቦምብ ጥቃት ደርሷል። በጥቃቱም እስከ 18 የሚደርስ ሰዉ ተጎድቷል።ተመሳሳይ የቦምብ ጥቃት በታህሳስ 22/2008 በዲላ ዩንቨርስቲ ተከስቶ 3 ሰዎች ሲሞቱ 6 መቁሰላቸዉ ታዉቋል። ዜጎች በነቂስ ድርጊቱ የህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ ነዉ የሚል መግባባት ላይ የደረሱ ይመስላል። ይህንኑ ለማረጋገጥ እስኪመስል ድረስ ዊኪ ሊክስ የተባለዉ የመረጃ አነፍናፊ ድረ ገጽ በበመስከረም5/2004 የኢትዮጵያ መንግስት እራሱ ቦምብ አፈንድቶ በኤርትራና በኦነግ እንደሚያላክክ አዲስ አበባ ከሚገኘዉ የአሜሪካ ኤምባሲ አፈትልኮ የወጣ መረጃን ዋቢ በማድረግ ለአለም ህዝብ አሳዉቋል። ታዲያ ህወሃት ወራሹ መንግስት እንደምን በጸረ ሽብር ዘመቻ ሁነኛ ስልታዊ አጋር ሊሆን ይችላል?
ከብሔራዊ ጭቆና ወደ ብሔራዊ ድል
ህወሃት መራሹ መንግስት በእምነት ጉዳይ ጣልቃ እንደሚገባ ክስ ይቀርብበታል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ዉስጥ ጣልቃ ገብቷል የሚል ለአመታት የዘለቀ ብሶት አለ። ኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች መጤ አንጃ አምጥቶ ጫነብን ብለዉ በመቃወም አለም አቀፍ ሰላማዊ ንቅናቄን ጀምረዉበታል።ህወሃት የአገሪቷን ሐብት ተቀራመተዉ፣ጥቂቶች ሐብታም ሲሆኑ ሚሊዮኖች በድህነት ማቀቁ የሚለዉ እሮሮ በሰፊዉ ይሰማል። አገሪቷ ዉስጥ የተንሰራፋዉ የርሃብ አደጋ በተፈጥሮ ክስተት የመጣ ቢሆንም የመልካም አሰተዳደር እጦት ርሃቡን የከፋ እንዲሆን አድርጎታል የሚለዉ ህዝባዊ ብሶት በሐዘና በሲቃ የሚሰማ ነዉ። የኢትዮጵያን ድንበር ቆርሶ ለሱዳን ለመስጠት የኢትዮጵያ መንግስት መስማማቱ የአገርን ሉዓላዊነት አስደፈረ የሚል ብሔራዉ ቁጭትን ፈጥሯል።በአገሪቷ ላይ የተንሰራፋዉ የመሬት ቅርምት ዜጎች በጫንቃቸዉ ላይ ሊሸከሙት ከሚችሉት በላይ ሆኖ እየተንገፈገፉበት ነዉ።
የኦሮሞ ተማሪዎች “መሬቴን አላስነጥቅም!” የሚለዉ ንቅናቄ አገራዊ ሆኖ ስርዓቱን ለመናጥ የበቃ ነዉ።ህወሃት ይህንን ሰላማዊ ንቅናቄ ለመቀልበስ በሰላማዊ ዜጎች ላይ አጋዚ በሚባለዉ ቅልብ ጦሩ የሚወስደዉ ዘግናኝ እርምጃ ህዝቡ ወደ “ህዝባዊ እንቢተኝነት” እንዲያመራ እየዳረገዉ ነዉ። ወልቃይት ጸገዴዉ ተገድጄ ትግራይ ዉስጥ ተካለልኩ ወደ አማራ ክልል ልመለስ በማለት የማንነት ንቅናቄን ጀምሯል። የጎንደሩ ገበሬ በደሙ የዋጀዉ መሬት ለሱዳን ሊሰጥ በመሆኑ እምቢኝ አሻፈረኝ ብሎ እየተነሳ ነዉ። አኝዋኩ መሬቴ ለባእዳን ተሽጦ በግፍ ተገደልኩ፣በግፍ ተፈናቀልኩ እያለ ነዉ። አርበኞች ግንቦት 7 በጦርነት ህወሃት መራሹን መንግስት እጥላለሁ ብሎ እየተዋደቀ ነዉ።
ብሶት የማይሰማበት የኢትዮጵያ ክልል የለም።ዜጎች ህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ ለ25 አመታት ባንሰራፋዉ አምባገነናዊ ስርዓት ተንገፍግፈዋል።
የማይቀር ህዝባዊ እምቢተኝነት ከፊት ለፊት ተጋርጧል። አሜሪካንም ሆነች ሌሎች ሐያላን አገራት ለህዝባዊ ጩኸት ‘ጆሮ ዳባ ልበስ’ ያለዉን ህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ ጣል-ጣል ቢያረጉ አይገርምም። የሚገርመዉ ‘ከማይታወቅ መልአክ… የሚታወቅ…’ ብለዉ በህወሃት ላይ ተስፋ ቢያረጉ ነዉ። አሜሪካንም ሆኑ ሌሎች በኢኮኖሚ የበለጸጉ አገራት ቅድሚያ ለብሔራዊ ጥቅማቸዉ ነዉ የሚሰጡት። አገራቱ ብሔራዊ ጥቅማቸዉ ህወሃት ጋር አለመኖሩን ቢረዱትም ያቺን የመጨረሻዋን ሰዓት የሚጠብቁ ይመስላል። ታዲያ!…ዉድና ጠቃሚ የጦር መሳሪያዎቻቸዉን ወደ ሌላ ቦታ መዉሰዱ መጨረሻዉ እየጀመረ አይመስልምን? “የመጨረሻዉ መጀመሪያ!” ለማንኛዉም ልብ ያለዉ ልብ ይበል።

Monday, December 28, 2015

Ethiopia Arrests Second Journalist in a Week, Rights Body Says (By William Davison, Bloomberg)

Ethiopian authorities arrested two journalists in the span of one week, the Committee to Protect Journalists said, asking the East African nation to allow for greater openness.
Getachew Shiferaw, editor in chief of Negere Ethiopia online newspaper, was arrested on Dec. 25, following the Dec. 19 detention of Fikadu Mirkana, an anchor at state-run broadcaster Oromia Radio and TV.
An Ethiopian court granted permission to hold him for 28 days for interrogation after which he is likely to be charged under the nation’s anti-terrorism law, according to the CPJ. The rules criminalize any reporting that authorities might consider encouraging to causes or groups the government labels as terrorist.
“Ethiopia prides itself on development, but economic growth is a hollow achievement if the public does not enjoy fundamental human rights such as the right to receive and share information and divergent viewpoints,” Sue Valentine, the CPJ’s Africa coordinator, said in an e-mailed statement.
Ethiopia’s police also detained Bekele Gerba, a leading opposition figure from the Oromo ethnic group that’s been protesting against an urban development plan over the last month, according to a government spokesman. 
Bekele and three other detained leaders of the Oromo Federalist Congress, or OFC, are suspected of inciting violent demonstrations against the expansion of the capital, Addis Ababa, into Oromia regional state, Communications Minister Getachew Reda said.

Oromo Opposition

“They’re suspected of committing crimes and conspiring to organize mobs to destroy property,” he said by phone from the capital on Thursday.
Security forces killed 82 unarmed Oromo demonstrators during the protests that began last month and spread across Oromia, Ethiopia’s most-populous region that surrounds Addis Ababa, according to the OFC. The government is still collecting information on fatalities and vandalism, Getachew said.
Amnesty International said last October that 5,000 Oromos had been illegally detainedfor political reasons since 2011. Bekele Gerba was released from prison in April after serving less than three years of an eight-year sentence for working with the banned Oromo Liberation Front. 
The arrests on Thursday are part of another widespread crackdown against Oromo political activists and demonstrators, said Merera Gudina, the OFC’s leader. “I think the government is very angry because millions of people are protesting for their rights across Oromia, so they are trying to punish the opposition,” he said by phone from Addis Ababa on Thursday.

Saturday, December 26, 2015

Oromo protests set to continue (By Deutsche Welle )

In an interview with DW, a spokesman of the Ethiopian Federal Democratic Unity Forum accused the government of abusing the country's constitution with its plans to expand the capital Addis Ababa.

A crowd of Oromo protesters
Violence and chaos gripped Ethiopia this week as thousands of demonstrators took to the streets in protest against government plans to expand the capital Addis Ababa. Human Rights Watch said at least 75 people were killed in a bloody crackdown by heavily armed security forces. The demonstrations have spread to several towns since November, when students spoke out against plans to expand the capital into Oromia territory, a move the Oromo people consider a land grab. DW spoke to Merara Gundina, chairman of the opposition Oromo Federal Congress, in Addis Ababa.
DW: What exactly are you demonstrating against?
Merara Gundina: The Addis Ababa Master Plan is part of a larger land grab by the Ethiopian government around Addis Ababa, which has displaced not less than 200,000 people. Secondly, under federalism all the boundaries are being eroded by the ruling party which is bent on taking the land. People are very angry with the government and people who wanted to see change are frustrated.
Under the Ethiopian constitution all land belongs to the state, with people living there legally considered tenants. Doesn't this allow the government to carry out any developments that may serve the interests of all Ethiopians?
No, no, the government is misusing it. The constitution says the land belongs to the public so it doesn't allow the government simply to tell the people "go away" and it takes the land. No, it says there are bonds of state in the name of the people and there are individuals owning the land. It is the ruling party that is misusing the constitution. In fact, the state itself is privatising the country.
We understand you have vowed to continue the demonstrations despite the killings and Prime Minister Hailemariam Desalegn declared on television that the government would act without mercy. Is it not better to solve these issues through talks?
We continue to support the cause of our people. We continue our peaceful struggle. We cannot be intimidated as the government has done. We have popular support, we have millions of people behind us. The government cannot silence us easily. We are following the constitution but we are against the arbitrary misuse of the constitution by the ruling party. Our people will continue.
Is it true that your organization is getting support from outsiders?
The diaspora is far away. It's school kids, high schools and universities and the government is simply accusing the left and the right. Probably the diaspora is very active in the media because the local media are totally controlled by the government. We have no access to the media and the diaspora have some media outlets and they report what is happening in the country. But a diaspora of a few thousand cannot move millions of people.

Friday, December 25, 2015

ለሱዳን ሊሰጥ ነው ስለተባለው መሬት (ፍቅሬ ቶሎሳ ጅግሳ፥ፒ ኤች ዲ፥ (የሁማኒቲስ ፕሮፌሰር)

መንግሥት ለሱዳን ሊሰጣቸው ነው የተባሉት አሁን በጎንደር አና በቤንሻንጉል አካባቢ የሜገኙት የእነ ኦሜድላና ጋምቤላ መሬቶች በአውነት የማን ናቸው? ያለጥርጥር የኢትዮጵያ ናቸው። ለምን እንደዚህ እንዳልኩ ዝቅ ብዬ አስረዳለሁ። መሬቶቹ በታሪክ የሱዳን ነበሩና ለሱዳን ይሰጡ የሚሉት የኢትዮጵያ ባለስልጣናት መሬቶቹን ለሱዳን ለመስጠት የሚያቀርቡት ምክንያት "በ በሱዳን የእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ጊዜ የእንግሊዝ መንግሥት ተወካይ የሆነ አንድ ሻለቃ የወሰን ምልክቱን የተከለው እዛ አካባቢ ነው፤ቀድሞ አፄ ምንይልክ በዚህ ተስማምተው፥ በሁዋላ ደግሞ አፄ ኅይለሥላሴ እና ደርግም ይህን አፅድቀውታል፤" የሚል ነው። በሌላ አነጋገር፥ በታሪካዊ ምክንያት ነው። እዚህ ላይ አንድ አስቂኝ ታሪክ ታወሰኝ። አንድ እንግሊዛዊ ከሱዳን የኢትዮጵያን ድንበር ተሻግሮ የዱር እንስሳና አውሬ ለማደን በሚል ፈሊጥ ሲዘዋወር ለስለላ ነው ብለው በጠረጠሩት የሃገሬው ተወላጆች ተገሎ እዛው ተቀበረ። ታዲያ ይህን ሰበብ አድርጎ አንድ እንግሊዛዊ መኮንን (ምናልባትም እላይ የተጠቀስው እብድ ሻለቃ) ያ አካባቢ በሞላ ለእንግሊዝ መንግሥት ሊሰጥ ይገባል፤አለ። በምን ሂሳብ ተብሎ በአባ መላ (ፊታውራሪሃብተጊዮርጊስ ዲነግዴ) ተጠየቀ። አንድ የእንግሊዝ ዜጋ ሞቶ እዚህ ስለተቀበረ፤ሲል መለሰ። አባ መላም ከትከት ብለው ስቀው፥እሺ ደግ ነው፤አንድ የእንግሊዝ ዜጋ ሞቶ እዚህ ስለተቀበረ ይሄን ሁሉ መሬት ለናንተ እንሰጣችሁአለን። የአፄ ቴዎድሮስ ልጅ ልዑል ዓለማየሁ ለንደን ውስጥ ሞቶ እዛው ለንደን (ዌስትሚኒስትር አቢ) ስለተቀበረ እኛ ደግሞ ለንደንን እንረከባችሁአለን። በዚህ ከተስማማህ ውል መፈራረም እንችላለን፤ ብለው አሾፉበት። ከዛ ቦታ በቅፅበት ዳብዛው ጠፋ።
ስለታሪክ ካወሳን ዘንድ፥ ይሄ ዛሬ ሱዳን የተባለው ምድር ሁሉ ቢያንስ ለ 4000 ዓመታት ያህል የኢትዮጵያ ግዛት ነበር።ጥንት የሚታወቀው ኑብያ ተብሎ ነበር። ኖባ በተሰኘው የኩሽ ዘር ስም። መናገሻውም መርዌ ነበር። የዛሬ 2900 ዓመት ግን ሱዳን ይባል ጀመር። ይህ ስም የወረደው ከአፄ አክሱማይት እናት ከንግሥት ሳዶንያ ነው። እሱ በህፃንነቱ የግብፅ ፈርኦን ሆኖ እስከሚያድግ ድረስ እስዋ በ 350,000 የአማራ ሰራዊት ታጅባ ዙፋኑን እየጠበቀች በሱ ስም ግብፅን፥ ሊብያን እና የዛሬውን ሱዳን ታስተዳድር ነበር። በዚህ ምክንያት፥ ከሳሃራ በርሃ በታች የአለው ምድር በሞላ ሳዶንያ ተባለ። ቀስ በቀስ ደግሞ ሱዳን። እንዳውም ኑብያ ውስጥ የነበረው መርዌ ለዛ አካባቢ እንደ ዋና ከተማ ሆኖ ያገለግል ነበር። ቢያንስ 14 የኢትዮጵያ ሴቶች ህንደኬ በሚል ማእረግ በንግሥትነት በተከታታይ ዛሬ ሱዳን፤ ግብፅና ሊብያ የሚባሉትን ሃገሮች ለ 1000 ዐመት ያህል ገዝተዋል። ለመጨረሻ ጊዜ የኑብያ ንጉሥ የነበሩት በ 16ኛው ክፍለ ዘመን የኖሩት አፄ ፋሲል ነበሩ። ከኑብያ ብቻ ሳይሆን ከስናር (ከካርቱምብዙያልራቀ ስፍራ) ድረስ የወርቅ ግብር ይመጣላቸው ስለነበር አዝማሪ አንዲህ ሲል የሱዳን ገዥነታቸውን አረጋግጦላቸው ነበር፤-
                              ጎንደር ቢያጉረመርም ፋሲል ፈረስህ
                               ኑብያና ስናር ወርቁን ጫኑልህ፥
                               ሳሩን ተጠየፈ የፋሲል ፈረሱ፥
                               ክምር የሱዳን ወርቅ ገፈራው ነው ለሱ።
"ገፈራ" ማለት የፈረስ ምግብ ነው። ዛሬ ፉርሽካ የምንለው ዐይነት። እንግዲህ ይህ ግጥም፥ ሱዳን አስከ የዛሬ 500 ዐመት የኢትዮጵያ ግዛት አንደነበረች ይመሰክራል። በሁዋላ በዘመነ መሳፍንት አና ከዛ ትንሽ ቀደም ብሎ ኢትዮጵያ አየተዳከመች ስትሄድ ቱርኮች ያዝዋት። ቱርኮች ተዳክመው ለእንግሊዝ ለቀቁላት። እንግዲህ ከእጅ የወጣ ሃገር በታሪክ ሰነድ ወይም ማረጋገጫ የሚመለስ ቢሆን ኖሮ፥ መላው ሱዳን ለኢትዮጵያ በተመለሰ ነበረ። ከላይ አንደ ተረዳነው ሱዳን የኢትዮጵያ እንጂ ኢትዮጵያ የሱዳን ሆና አታውቅም። ታዲያ በምን ምክንያት ነው አሁን የኢትዮጵያን መሬት የጠየቀችው? እስዋ አፍዋን ምን ቁርጥ አርጉዋት ጠየቀችና? እስዋ በራስዋ ተነሳስታ ደፍራ መሬት አለኝ አላለችም። አሁን በአመራር ላይ የአሉት የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ደርግን በሚዋጉበት ሰዐት ሱዳን ለዋለችላቸው ውለታ ወሮታውን ሊመልሱላትና አሁንም ተቀዋሚዎቻቸውን እንዳታስተናግድ የሚከፍሉዋት ዋጋ መሆኑ ነው። ወዲህም መሬቱ ያለው በአማራ፥በቤንሻንጉል፥ በጋምቤላና በአሮሞ ክልሎች ስለሆነ የእኛን ምድር ስለማይመለከት ችግር የለውም ዐይነት ነው። ብሄራዊ ስሜት የሚባል ነገር ስለሌለ። መሬት በነፃ እንካ ከተባለ ማን ይጠላል? ስለዚህ ሱዳኖቹ እየፈነጠዙ ሊወስዱ አኮብኩበዋል።
አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው መንግሥት 1600 ኪሎሜትር ለም መሬት ለሱዳን ይገባታል ብሎ ጠበቃ የቆመላት እላይ የተጠቀሰው ቅኝ-ገዢ መኮንን በቸከለው ድንበራዊ ችካል ክሆነና በእንግሊዝ ቅኝ ገዥነት አገር ቅርጫ አንዲሆን ከተፈቀደ፥ እንዲሁም እንግሊዝ ያቀናው መሬት ሁሉ ለሱዳን ይቸር ዘንድ ከተፈረደ፥ የቀድሞው የአንግሊዝ ቅኝ ግዛቶች የነበሩት እነ ዩጋንዳና ሱዳን፥ ካስፈለገም እነ ናይጀሪያ ሁሉ ለሱዳን መሰጠት ይገባቸዋል ማለት ነዋ!!! የሆነ ሆኖ፥ ያ ሆፈፌ ቅዥተኛ እንግሊዝ ምኞታዊ ህልም አልሞ የፈለገውን ያህል የወሰን ድንጋይ ቢተክልና አፄ ምኒልክም አልተስማሙም እንጂ ቢስማሙለትና መሬት ቆርሰው ቢሸልሙትም አንኩዋን ያ ውል የሞተ ነው። ለምን ቢባል፥ ሱዳንን ዐለምና የተባበሩት መንግሥታትም ያወቃትና በታሪኩዋ ለመጀመሪያ ጊዜ ራስዋን ችላ የራስዋን ባንዲራ ያውለበለብችበት ዳር ድንበር አሁን የአለው ነውና። እኤአ በ 1953 ዐመተ ምህረት እንግሊዝ ግዛቴ ይሄ ብቻ ነውና ያንቺም ግዛትሽ ይሄው ነው ብሎ በዐስር ጣቱ ፈርሞ የተወላት መሬት ነው። እሱውም ከመከፈልዋ በፊት የነበረው የቆዳ ስፋቱ 2,505,813 ስኩዌር ኪሎሜትር የሆነው ነው። ከመከፈልዋ በፊት ሱዳን በቆዳ ስፋት ከአፍሪካ አንደኛ ነበረች። አሁን ሶስተኛ ነች። አሁንም ከኢትዮጵያ ትልቃለች ማለት ነው። የያዘችው ይበቃት ነበር። የኢትዮጵያን መሬት ለግሰናት በደቡብ ሱዳን የተወሰደባትን መሬት እንተካላት ካልተባለ በቀር። ሰጭና ነሽው አንግሊዝ ከተደረገና የእንግሊዝ መንግሥት ለክቶ፥ "አበጥሮ"፤ "አንጥሮ" ሁሉን አጣርቶ ራሱ በመጨረሻ ያረጋገጠው የሱዳን ምድር እላይ የተጠቀሰው ስፋት ከሆነ በምን ሂሳብ ነው አንግሊዝም ሆነ የተባበሩት መንግሥታት የማያውቁትን የኢትዮጵያን መሬት በ ህቡዕ ለሱዳን የሚለገሳት? አይገባትም አንጂ በ እርግጥ ሱዳን ይገባኛል የምትለው መሬት ከአላት ወደ ተባበሩት መንግሥታት ሄዳ ነው አንጂ አቤቱታዋን የምታቀርበው በስርቆሽ በር ነው እንዴ መሬት ቆርሳ የምትሮጠው? ወይንስ መሬቱን ከቦጨቀች በሁዋላ ወደ ተባበሩት መንግሥታት ቀርባ መርቁልኝ ልትል ይሆን? እስዋ ግን ወደ እዛ እስካሁን ያልሄደችው እኤአ በ 1953 እንግሊዝ ካስረከባት በቀር ሌላ መሬት ስለማይገባት "ወይጅ ወዲያ አትቀልጅ!" ይሉኛል፤ ብላ ፈርታ ነው። አለዛ ሱዳን ነፃ ከወጣች ጀምሮ መሪዎችዋ ከ ኢብራሂም አቡድ ጀምሮ እስከነ ኑሜሪ አና አሁን ያለውም አል በሺር የይገባኛሉን ጥያቄ ገና ድሮ ባቀረቡ ነበር። ሰብብ ፈጥረን ስለቀድሞ ውለታዋ እና ተቀዋሚዎቻችንን ስለምትገታልን እንዲሁ በነፃ እንቸራት ካልተባለ በቀር እንደ እውነቱ ከሆነስ ሱዳን፥ "ኢትዮጵያ ያዘችብኝ፥ ይገባኛል፤" የምትለው አንዲት ስንዝር መሬት የላትም። ከቅኝ ግዛት ነፃ ከወጡ በሁዋላ የአፍሪካ ሀገራት በሞላ የያዙት ድንበርና ወሰን የቅኝ ገዥዎችቸው አነዚህ ናቸው፤ ብለው ያረጋገጡላቸውን ብቻ ናቸው። ስለዚህ ሱዳን ከሌሎቹ የአፍሪካ ሃገራት
በምንም አትለይም። በመሆኑም ከኢትዮጵያ ልቀበል ይገባኛል ልትል የሚያስችላት ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ጥሪኝ አፈር የላትም። ስለ ኦሜድላ ብቻ እንኩዋን ብንዘክር፥ አፄ ኅይለሥላሴ በሱዳን በኩል ከስደታቸው ሲመለሱ ከ 5 ዐመታት በሁዋላ ለመጀመሪይ ጊዜ የኢትዮጵያን ሰንደቅአላማ ሰቅለው የአውለበለቡት ኦሜድላ ላይ ነበር። ይህን በሚያደርጉበት ጊዜም የ እንግሊዝ የቅኝ ገዢ ትልቅ ባለስልጣናት ለ ሰንደቅአላማዋ አክብሮት በተጠንቀቅ ቆመው መሬቱ የኢትዮጵያ መሆኑን ተቀብለው ይመለከት ነበር እንጂ "የሱዳን መሬት ላይ እንዴት ባንዲራ ያውለበልባሉ!" ሲል በንጉሱ ላይ ቅዋሜ አላሰሙም። ኦሜድላ የኢትዮጵያ ለመሆንዋ ከዚህ በላይ ምን ማረጋገጫ አለ? ታዲያ በምን ምክንያት ነው አሁን ይቺ ታሪካዊ ስፍራ ለሱዳን የምትሸለመው? ቀዳማዊ ኅይለሥላሤ ኦሜድላ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅአላማ ሲያውለበልቡ ጦሩን እንዲያቀነባብር በእንግሊዝ መንግሥት ተሹሞ አብሮአቸው በሱዳን በኩል የገባው ሜጄር ዊንጌትም ታዛቢ ሆኖ እጎናቸው ነበረ። ንጉሡን ተሽቀዳድሞ አዲስ አበባ የገባው ሎርድ ካኒንግሃምም እሳቸው ኦሜድላ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅአላማ እንዳውለበልቡ አሳምሮ ያውቅ ነበር። እነዚህም ሁለት ታላላቅ የእንግሊዝ መንግሥት ተወካዮች ኦሜድላ የኛ ናት አላሉም። የሆነ ሆኖ እውነት እንግሊዝ ከ አፄ ምንይልክ ጋር ተዋውሎ ከነበር እሱው እንግሊዝ የመሬት ይገባኛል ጥያቄውን ያቅርብልን እንጂ ያልተዋዋልናት ሱዳን ምን አገባት? ከሱዳን ሳንዋዋል እንዴት ሱዳን የተዋዋልነው ይከበርልኝ፥ ልትል ትደፍራለች? ይህን ጥያቄ ሊያነሳ የሚችል አንግሊዝ ብቻ ነው። ነበርም። ግን እንግሊዞች አላነሱም። ምክንያቱም ቀላል ነው። የዚህ ዐይነት ውል ከአፄ ምንይልክ ጋር ስላተፈራረሙ። ተፈራርመው ቢሆን ኖሮ መጠየቅ ብቻ አይደለም፥የተፈራረሙበት ቀለም ሳይደርቅ መሬቱን እጃቸው ያስገቡ ነበር። ስላልተፈራረሙ ይህን አላደረጉም። የሱዳንን ነፃነት እንግሊዞች ሲፈቅዱም የተባለውን መሬት የኔ ነበር ብለው ወደ ሱዳን አላዘዋወሩም። አሁን ያለውን መሬት ብቻ ነው ትተውላቸው የሄዱት።አሱም ለሁለት ተከፍሎባቸዋል። ከአንግሊዝ የተረከቡትን መሬት እንኩውዋን በቅጡ መያዝ አቅቶአቸው "የቆጡን አወርድ ብላ የብብትዋን ጣለች፤" የተባለው ተረት በነሱ ላይ ተፈፅሞባቸዋል። የራሳችውን አጥብቀው መያዝ ሳይችሉ የኛን መሬት መከጀላቸው ማስቆጣት ብቻ ሳይሆን ያስደንቃል። እንግዲህ እንግሊዝ ከአፄ ምንይልክ ጋራ መሬትን አስመልክቶ ላለመዋዋሉ ሶስት ማስረጃዎች አሉ ማለት ነው። አንደኛ፥ የተባሉትን መሬቶች ቀደም ሲል እጁ ባለመክተቱ፤ ሁለተኛ፥ ንጎሱ ኦሜድላ ላይ ሰንደቅአላማችንን ሲሰቅሉ አለመቃወሙ፥ ሶስተኛ፥ ሱዳንን ለቆ ሲሄድ ለሱዳን ከተወላት የተባበሩት መንግሥታይ ባፀደቀላት ዳር ድንበር ውስጥ እነዚህን ሁሉ የኢትዮጵያ መሬቶች በካርታም ሆነ በፅሁፍ ባለማካተቱ። በነዚህ ሶስት ማስረጃውች ምክንያት እሩቅ ሳንሄድ፥ ሰነድ ለማግኘት አፈር ሳንቆፍር እና ድንጋይ ሳንፈነቅል ምንይልክ እና እንግሊዝ አንዳችም የመሬት ውል እንዳልተፈራረሙ እናረጋግጣለን። ተፈራርመዋል የሚል እስቲ ሰነዱን ያቅርብልን!!! ደግሞም ቢፈራረሙም እንኩዋን ውሉ የቅኝ ገዥዎች ሰለሆነና ምንይልክም ሆነ ማንኛውም መሪ የአትዮጵያ መሬት የግል ንበረቱ ስላልሆነ መሬት ለባእዳን ሰጥቻለሁ ቢል አይፀናም።
አፄ ምንይልክ ተስማምተውበት፥ አፄ ኅይለሥላሴ እና ደርግ ያፀደቀውን ነው እኛ በ ተግባር የምናውለው፤ ሲል ኢህአዲግ ደጋግሞ ተናግሮአል። ይህን መሰረት በማድረግ እኔ ብዙ ምርምር አካሂጄ ሁለቱ አፄዎችና የደርግ ሊቀመንበር የነበሩት ኮረኔል መንግሥቱ ኅይለማርያም ለሱዳን መሬት ለመስጠት የተዋዋሉበት አንድም ሰነድ አላገኘሁም።ምክንያቱም ስላልነበረ። ስለ ሌለም። አሁን በህይወት የአሉት ኮሎኔል መንግሥቱም አንድም የዚህ ዐይነት ውል ከሱዳን ጋር እንዳልተፈራረሙ አበከረው መስክረዋል። ይልቁንም አኔ ያገኘሁት መረጃ፥ አውሮፓውያን መንግሥታት ለብቻቸው ተሰብስበው አፍሪካን ለመቀራመት ያደረጉትን ውል ለአፄ ምንይልክ ነግረው የኢትዮጵያን ነፃነት ግን አንደሚያስጠብቁ ቢገልፁላቸው፥ "እኔ በሌለሁበት እናንተ ተሰብስባችሁ ያደረጋችሁትን ውል በፍፁም አልቀበልም፤ የኢትዮጵያን ነፃነት አናስጠብቃለን ሰለአላችሁት ግን አመሰግናለሁ፤" በማለት ተንኮላቸውን ውድቅ ማድረጋቸውን የሚያሳይ ነው። በነገራችን ላይ፤ አፄ ምንይልክ እንኩዋን ለሱዳን መሬት ሊሰጡና በሰላም ኢትዮጵያ ውስጥ ይኖሩ የነበሩት የውጭ ሀገር ሰዎች መሬት አንዲገዙ አይፈቅዱላቸውም ነበር። አላደረጉትም እንጂ ሶስቱም መሪዎች አድርገውትም እንኩዋን ቢሆን፤የኢትዮጵያን ህዝብ መሬት አንስተው ለባእዳን ለመቸር ምንም መብት አልነበራቸው። ኢትዮጵያ፥ እንዲያስተዳድሩዋት አደራ የተሰጠቻቸው ምድር እንጂ እንዳሻቸው ለፈለጋቸው አገር ገፅበረከት አድርገው የሚለግስዋት የግል ንብረታችው አልነበረችምና። አሁን ያለውም መንግሥት አንዲሁ የኢትዮጵያን መሬት ገምሶ ለባእዳን ለመቸር ከቶም አንድም ህገመንግሥስታዊ ነፃነት ወይም ስልጣን የለውም። በጉልበቱ ካልሆነ በቀር። ረጅሙን ታሪካችንን ወደ ሁዋላ መለስ ብለን ብናስተውል፥ ባለፉት 5300 ዐመታት ኢትዮጵያን የመሩት መንግሥታት ድንበር ከማስፋት በቀር መሬታቸውን እንደ አንጀራ ቆርሰው ለባእዳን ሲቸሩ በፍፁም ተስተውሎ አያውቅም። አሁን ከአለው መንግሥት በስተቀር።
እዚህ ላይ ባድመ ይታወሰናል። ባድመ ባድማው ደረቁ መሬት ከአትዮጵያና ኤርትራ በኩል ወደ 150000 ገደማ ወይም ከዛ በላይ ምስኪን ሰዎች በከንቱ አስጨረሰ። ከዚያ አልጀርስ ላይ ለኤርትራ ይገባታል ይሰጣት፤ ተብሎ ተፈረደላት።ባድመ እስካሁን በ ኤርትራ እጅ ውስጥ አልገባችም። ለምን? የትግራይ መሬት ውስጥ ስለሆነች የማትነካ፥ የማትገሰስና የተቀደስች ሆና ወይስ በሌላ ምክንያት? ሰፊ መሬት አለኝ ብሎ ከማውራት በቀር ለማንም የማይጠቅመውን ጠፍ መሬት አንሰጥም ብሎ ይዞ፥ ለመሬት ብላ ከኛ ላልተዋጋችው ሱዳን ለምለም ምድር ገምጦ ለመቸር መቸኮል ምን ይባላል? ይህ ለሰሚው ግራ ነው። ባድመም በኤርትራ ላትወስድ የቻለችው፥ "ትግራይ ሀገርህ ተወራለችና የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! ተነሳ!" ተብሎ በተጠራው የሀገር ማዳን ጥሪ መሰረት፥ "ጉዳዩ እኔን አይመለከተኝም ይህ የትገራይ መሬት ነው፤" ሳይል በብሄራዊ ስሜት የነደደው ቆራጡ የኢትዮጵያ ህዝብ አጥንቱን ከስከሶ፤ ደሙን አፍሶ፤ንብረቱን አጉድሎ ባደረገው ተጋድሎ ነው። ትግራይ ስትወረር የኢትዮጵያ ህዝብ ፥ "ወይኔ ሃገሬ!" ብሎ ደሙን ሲያፈስ ባድመ የመጨረሻው እንጂ የመጀመሪያው አይደለም። ከዛ በፊት ጣልያን ከማንም አስቀድሞ ትግራይን በወረራት ጊዜ በመቀሌ፥ በአምባላጌ፥በአድዋ እና በማይጨው በ 40 ዐመታት ልዩነት ውስጥ ሁለቴ ከፍተኛ መስዋእትነት ከፍሎአል። ለዚህ ሁሉ ውለታው አፃፋው ይሄ ነውን? እባካችሁ ሰከን ብላችሁ ነገሩን አስቡበት። ይህ ድርጊት በትውልድ ያስወቅሳችሁአል። ጠንቁ ለልጆቻችሁና ለልጅ ልጆቻችሁ፤ እንዲሁም ለዘራችሁ ይተርፋል። ለስልጣን ያበቃችሁ የትግራይ ህዝብ ሳያቀር በአደራጎታችሁ ያፍርባችሁአል። የኢትዮጵያ ህዝብ ዛሬ አቅም ባይኖረው ነገ ሊጠነክር ይችላል። ሳይወድና ሳይፈቅድ መሬቱን ሱዳን አሁን ብትወስድበት እንኩዋን ነገ ሲጠነክር ተዋግቶ ያስመልሰዋል። በዚህ ሳቢያ አሁን ልትጠቅምዋት ያሰባችሁአት ሱዳንም ሰላም አታገኝም። የ እናንተም ስም በክፉ ተነስቶ አፅማችሁም ሲወቀስ ይኖራል። ስለዚህ ሱዳንን በሌላ በሌላ ነገር ካስዋት እንጂ የስንት ሰማአታት ወገኖቻችን ደም እና ላብ የአለማውን መሬታችንን አሳልፋችሁ በብላሽ አትስጡ። ለሱዳን ካሳ፥ አፍንጫዋ ስር የተገነባላት የአባይ ግድብ መች አነሳት? በዚህ የኢትዮጵያ ህዝብ ገንዘቡን በከሰከሰበት ግድብ ከማንም በላይ ተጠቃሚዋ ሱዳን አይደለችንምን? ግድቡ ይበቃታል፤ መሬቱ ይቅርባት። ብቻችሁን ይህን መወሰን ካስቸገራችሁ ደግሞ ፓርላማችሁና የኢትዮጵያ ህዝብ ይምከርበት። ለይስሙላስ ቢሆን ፓርላማ አለ አይደል? እንዲህ ዐይነቱ ትልቅ የሀገር ሉአላዊነት ጉዳይ ሀገር ሳይመክርበትና ህዝብ ሳይወስንበት አንዴት በዝግ ጉዋዳ ይካሄዳል? ባድመ አንዳትወሰድ የተረባረባችሁትን ያህል አና ለኤርትራ አንዳይሰጥ የምትተጉትን ያህል፥ እባካችሁ አሁን ሱዳንን የሚያዋስናትን ሁሉ የኢትዮጵያ ዳር ድንበር ለሱዳን ከመቸር ታቀቡ። በውኑ ከዚህ ከታቀባችሁ፥እናንተም፤ ልጆቻችሁም፥ ዘራችሁም፥ አንዲሁም በመቃብር ውስጥ የሚኖረው አፅማችሁም ከመወቀስና ከመረገም ይተርፋል። ጆሮ ያለው ይስማ። ልብ የአለው ልብ ይበል።

Tuesday, December 8, 2015

ጃዋር መሀመድን ለፍርድ ለማቅረብ እንቅስቃሴ መጀመሩን ተገለጸ

የጃራ ሽባብ ተበሎ በሚጠራው የኦሮሞ የእስልምና አክራሪዎች ቡድን መሪ የሆነው ጃዋር መሀመድ በክርስቲያኖችና በኢትዮጵያውያኖች ላይ የአለምን አቀፍ ህግን በመጣስ ዘርን ከዘር ፣ሀይማኖትን ከ ሀይማኖት ለማጫረስ አንዳንድ ተራ ነገሮችን ሰበብ በማድረግ በከፍተኛ ደረጃ በሳይበር በአገር ውስጥ በተለይም በዲያስፖራ ለተጀመረው የጥላቻ ቅስቀሳ ለማስቆምና ግለሰቡን ወደ ፍርድ ለማቅረብ የህግ ባለሙያዎች እየተሰባሰቡና ምረጃዎችንም በመሰብሰብ ላይ ናቸው።የአለም አቀፍ ህግ ዘር ማጥፋትን ሳይሆን ቅስቀሳን ማድረግ በራሱ ትልቅ ወንጀል ነው።

The United Nations’ Genocide Convention outlaws not only acts of genocide but “incitement” to genocide, an egregious offense whether or not genocide has yet occurred. The convention’s goal, of course, is to prevent genocide before it takes place. Those who incite genocide, and those who defend them, often invoke the freedom of speech. But no free-speech law condones threats of mass murder. The Nuremberg tribunal convicted and executed Nazi newspaper publisher Julius Streicher for inciting the murder of Europe’s Jews, even though he hadn’t committed murders directly.

Generally speaking, “incitement” means encouraging or persuading another to commit an offense by way of communication, for example by employing broadcasts, publications, drawings, images, or speeches. It is “public” under international law if it is communicated to a number of individuals in a public place or to members of a population at large by such means as the mass media. Among other things, its “public” nature distinguishes it from an act of private incitement (which could be punishable under the Genocide Convention as “complicity in genocide” or possibly not punishable at all). public incitement to genocide can be prosecuted even if genocide is never perpetrated. Lawyers therefore classify the infraction an “inchoate crime”: a proof of result is not necessary for the crime to have been committed, only that it had the potential to spur genocidal violence.

ጃዋር እልቂትን ከመቀስቀስ አልፎ ግድያው እንደት እንደሚፈጸምም በተለያዩ ስብሰባዎች ላይ ገልጽዋል።ይህን ጉዳይ በተመለከተ ዝርዝሩን ይዘን እንቀርባለን።

==================================================================================

What is the Jara Shabaabes Movement ?
 Jara Shebab Movement is a movement lead by Jawar Mohammed , Abdi Fite,Mohammed Ademo, kedir Elmo,Aisha Ali, Arfasse Oromiyaa,Geresu Tufa,Jicha Hamid,Mohammed Sheka. This movement primarily focuses on incitement of hate and genocide among different ethnic and religious communities in Ethiopia and all over the world. They primarly targeting none Muslims and None oromos to some extent on moderate Oromos whom reject their narrow ,religious originated approach to Ethiopian present day problems. They coned Al Jazeera and some Arabs into believing that Oromos are Muslims who are oppressed by Christians.

The Oromo Jara Shebabe group “Oromo First” campaign has been exclusivity movement that wants to target Christians under the guise of Oromo people’s question for justice and equality. It is very vital that we negate such teaching and uproot it from the roots. Radical Islam knows not tolerance, compromise, democracy, and so forth. It is an ideology based on fanaticism that is myopic. The main agenda of such ideologies is to dominate, suppress, and oppress other societies and religions around them. Complete control is the idea behind such radicalism. This type of teaching has and is being propagated by groups like Oromo extremists and other radical Islam followers who want nothing but dominate and submerge everyone else. The ethnic cleansing, Church burnings, killings, and intimidations are all part of the wider strategy of these extremist Oromo Islamists and nationalists . The ongoing recent rhetoric exemplifies that where they have been calling out for the killing and ethnic cleansing of Amharas solely because they are Christians. What we must understand is that this will not stop with Amharas only. Once Jawar and his followers prosecute the Amahras, they will also come for Oromo, Sidama, Hadiya, Wolyta, etc… Christians. All one has to do is carefully examine Jawar’s speeches, statements, and writings. In one of his speeches given before a Muslim audience, he specifically stated that where he lives that many of the Oromos residing are Muslims, and therefore, if any Christian attempted to speak or exercise his or her right, they would be decapitated without question. In another video, Jawar specifically states, “Ethiopia out of Oromia.” This is in reference to so called Ethiopians to get out of so called Oromo regions. In other words, he is basically calling for an ethnic cleansing. There is many data to the open public for one to examine how these extremists are gaining momentum. It is the responsibility of everyone to expose such extremists because in the end the losers of this war will be everyone.


Tuesday, May 26, 2015

Merera Gudina says ballot boxes were stolen in organized robbery (By Aaron Maasho)

ADDIS ABABA (Reuters) - African Union observers said on Tuesday that Ethiopia's parliamentary election held on Sunday was credible except for a few irregularities, but the opposition dismissed the vote as marred by violations including ballot box theft.
Provisional results in Africa' second most populous nation are due later this week and few expect anything but a landslide for the ruling Ethiopian People's Revolutionary Democratic Front (EPRDF) coalition, in power since ousting dictator Mengistu Haile Mariam in 1991.
Prime Minister Hailemariam Desalegn, who took over after EPRDF's long-serving leader Meles Zenawi died in 2012, has pushed on with EPRDF's highly-centralised statist economic model credited with turning around the fortunes of a country once ravaged by war and famine.
But the opposition -- which has one seat in the outgoing 547-member parliament -- accuses the government of crushing dissent, limiting free speech, and muzzling the press. The EPRDF denies this, saying the political space is open for all.
"The African Union Election Observation Mission (AUEOM) concludes that the parliamentary elections were calm, peaceful, and credible as it provided an opportunity for the Ethiopian people to express their choices at the polls," former Namibian President Hifikepunye Pohamba, the head of the AU mission, said.
Pohamba said 59 members from 23 African countries visited 356 polling stations. Ethiopia did not invite Western observers to this election. About 37 million out of Ethiopia's 96 million people registered to vote.
The observers said no major incidents occurred and that they could vouch for the secrecy of the vote in 95 percent of the polling stations it observed.
However, the mission said that in 21 percent of all stations it visited, station officers violated rules by failing to display empty ballot boxes before the official start of the elections.
It also noted that a few voting centres had opened ahead of time, though staffers claimed this was due to requests from voters.
WITCH-HUNTS
Merara Gudina, deputy chairperson of the opposition Medrek coalition dismissed the AU report, claiming the body had failed to report on violations in many constituencies.
Merara told Reuters that security personnel had launched a "witch-hunt" on the eve of the vote by arresting his group's observers. He also said ballot boxes had been stolen in his constituency outside the western town of Ambo some 130 kilometres (81 miles) from the capital.
"The whole process was a farce. In my constituency, we do not even know what happened to over 80 percent of the ballot boxes right after the polls closed, " he said. "It was organised robbery."
The electoral board -- which is set to announce provisional results before the end of the week -- was not immediately available to comment on the claims.
On the day of the vote Hailemariam rejected opposition claims of foul play.
"They have been campaigning freely. There has not been any repression as far as this is concerned," Hailemariam told Reuters on Sunday in his constituency in Gununo, a town 330 kilometres southwest from the capital.
Ethiopia's economy has been one of the fastest growing in Africa and beyond. The World Bank forecasts growth of 10.5 percent in the year starting in July.

Friday, April 3, 2015

የት ሂዱ ነው? ፕሮፌሰር መስፍን

አንድ
269706_236781196336481_2576526_n
የት ሂዱ ነው?
ዓለም ሁሉ ጠላን፤ በየትም አገር እየሄድን ‹‹የሙጢኝ!›› ከራሳችን መሬት በጉልበት እየተነቀልን፣ ከራሳችን ቤት እየተባረርን፤ ከተወለድንበትና ከአደግንበት አካባቢ እየተፈናቀልን፣ ጭራውን ቆልምሞ እንደሚሮጥ ባለቤቱ እንዳባረረው ውሻ በአገኘነው አቅጣጫ እየሮጥን፣ እጃችንን እያርገበገብን ‹‹የሙጢኝ!›› እንላላን፤ የፈራነውን ሞት በየመንገዱ እናገኘዋለን፤ ሞትን ሸሽተን ሞትን ያጋጥመናል፤ የሞቱ ልዩነት አይታየንም፤ በየመንገዱ የሚያጋጥመው ሞት የውርደት ሞት ነው፤ የብቸኛነት ሞት ነው፤ ዘመድ-ወዳጅ ለቀብር የማይገኝበት ሞት ነው፤ ሠለስት፣ አርባ፣ ሙታመት የማይወጣበት ሞት ነው፤ ባዕድ ምስጥ ያላሳደገውን አካል የሚበላበት ነው፤ የሞት ሞት ነው፡፡
ኢትዮጵያውያንን ሁሉ ከአገር አስወጥቶ ባዶ መሬት ብቻ ይፈልግ ይመስል የወያኔ ሎሌዎች በማስፈራራት ሁሉም አገሩን እየተወላቸው እንዲሄድ ያቀዱ ይመስላል፤ ጥንት ኢሰመጉ በምሠራበት ጊዜ በየጊዜው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ሰዎችን በማስፈራራት ሰላማቸውን ለመረበሽ ወደስደት ወይም ወደወንጀል ተግባር የሚመሩ የወያኔ አባለች ነበሩ፤ አሁን እንደገና ብቅ ማለት ጀምረዋል፤ ሕጋዊ ሥርዓት እየላላ ጉልበተኞች በግላቸው ለዘረፋና ለቅሚያ እየተሰማሩ ይመስላል፡፡
ስለራሴ ላውራ፤ ከእኔ የሚፈልጉት ምን እንደሆነ እርግጠኛ አይደለሁም፤ የሚፈልጉት የምኖርበትን አፓርትመንት እንደሆነም አላውቅም፤ በእኔ ቤት ያለ ሀብት የሚባል ለወያኔ አገልጋዮች የሚጠቅም ሁለት የገብረ ክርስቶስ ስዕሎች ብቻ ናቸው፤ (በዚህ አጋጣሚ እነዚህን ስዕሎች ለመግዛት የሚፈልግ ያነጋግረኝ)፤ ከዚህ ሌላ ለወያኔ ዋጋ የሌላቸው መጻሕፍት ናቸው፤ ስለዚህም አሁን በእኔ ላይ የተሰነዘረው ጥቃት እኔን ወደስደት ለመግፋት የሚደረግ ሙከራ ይሆናል፤ በ1992 ግድም ተሞክሮ ነበር፤ አልሠራም፤ ዛሬ ይበልጥ አይሠራም፤ ለማናቸውም ምክንያቱን በትክክል ለማወቅ ባልችልም በእኔ ላይ ዘመቻ መጀመሩን አንድ በቅርብ ከማውቀው ወያኔ በትክክል ተረድቻለሁ፤ ይህንን ዘመቻ በመምራት ላይ ያለውንም ሰው ማንነት ተነግሮኛል፡፡
ይህ አገር የአንድ ጉልበተኛ ቡድን ነው ብዬ አልቀበልም፤ የአባቶቼና የእናቶቼ፣ የኤቶቼና የቅድማያቶቼ አጥንትና ደም የገነባው አገር ነው፤ ማንም ለስደት አይዳርገኝም፤ ማንም አስፈራርቶ ኢትዮጵያዊነት መብቴን መግፈፍ አይችልም፤ አልፈቅድለትም፤ በግልጽ በማያጠራጥር ቋንቋ ኑሮዬም፣ ሕይወቴም፣ ሞቴም እዚሁ ነው፤ ከኢትዮጵያ አፈር የሚለየኝ የለም፡፡
እኔን ለማጥቃት ላሰፈሰፉት ወያኔዎችና ሎሌዎቻቸው አንድ እውነት ልንገራቸው፤– በፈለጉትና በተመቻቸው መንገድ በእኔ ላይ በጉልበታቸው ግፍ ቢፈጽሙ ነገ በነሱ ላይ የባሰ ግፍ እንደሚደርስባቸው ይወቁት፤ ሁልጊዜም ከሕግ የወጣ ጉልበተኛነት ጉልበተኛነትን ያነግሣል፤ በመግደል ድል ይገኛል ብለው የሚያምኑ ወያኔዎች ትንሽ ቆም ብለው ያስቡ፤ በመሞትም ድል ይገኛል፤ በመሞትም ማሸነፍ ይቻላል፡፡
በእኔ ላይ የዘመተው ወያኔ ወይም ሎሌ ማናቸውም ሥራ ውጤት እንዳለው ማወቅ አለበት፤ አንድ ነገር አድርጎ ምንም ዓይነት ውጤት አያስከትልም ብሎ ማሰብ ድንቁርና ነው፤ ይህ የሳይንስ ሕግ ነው፤ For every action there is a reaction ይላል!

Thursday, April 2, 2015

Somali Islamists kill 147 in Kenya university massacre

View gallery
Garissa (Kenya) (AFP) - Masked gunmen from Somalia's Shebab Islamist group massacred at least 147 Kenyan students Thursday in a day-long college campus siege, the country's deadliest attack since the 1998 US embassy bombings.
Hurling grenades and firing automatic rifles, the gunmen had stormed the university in the northeastern town of Garissa at dawn as students were sleeping, shooting dead dozens before setting Muslims free and holding Christians and others hostage.All four of the gunmen wore suicide vests packed with explosives, detonating themselves in huge blasts as the dramatic assault finally ended after some 16 hours.
The government said at least 79 people were wounded in the assault near the lawless border with war-torn Somalia, several seriously, and there are fears the death toll may still rise.
In the final hour before darkness fell, Kenyan troops stormed a student dormitory where the gunmen were holed up as blasts and fierce gunfire rang out.
Interior Minister Joseph Nkaiserry said the four died detonating their suicide vests as soldiers burst in shooting, with Western security sources reporting that several soldiers and hostages may have died in the final blasts.
Troops then continued to search the campus for any possible insurgents until the siege was declared over late on Thursday, with the national disaster operations centre saying it had "ended with all four terrorists killed."
The attack was claimed by Al-Qaeda-linked Shebab fighters, the same insurgents who carried out the Westgate shopping mall massacre in Nairobi in September 2013, when four gunmen killed at least 67 people in a four-day siege.
Shebab spokesman Sheikh Ali Mohamud Rage told AFP the gunmen had taken non-Muslims hostage, and that their mission had been "to kill those who are against the Shebab."
- Senseless and barbaric -
The university siege marks the worst attack on Kenyan soil since the 1998 bombing of the US embassy in Nairobi by Al-Qaeda, when 213 people were killed by a huge truck bomb.
The United States condemned Thursday's attack in the "strongest terms", while UN Secretary-General Ban Ki-moon called for those responsible to "be swiftly brought to justice."
British Minister for Africa James Duddridge called the killings "senseless" and "barbaric", while the French presidency said it stood "ready to work" with Kenya in its fight against terrorism.
It was not clear if any of the students the Shebab said they had held were alive at the time of the final assault by troops. However, officials said over 500 students had been rescued from the fighting.
"Kenya is at war with Somalia," Rage said, referring to the thousands of Kenyan troops in Somalia as part of an African Union military mission.
Soldiers with tanks were deployed around the campus.
A $215,000 (200,000 euro) bounty was offered for the capture of alleged Shebab commander Mohamed Mohamud, a former Kenyan teacher believed to now be in Somalia and said to be the mastermind behind the Garissa attack.
The garrison town is around 150 kilometres (90 miles) west of Somalia and has been targeted in the past by militants from the Shebab.
- 'Gunmen shot indiscriminately' -
Police chief Joseph Boinet said "the gunmen shot indiscriminately" after storming the compound.
The sprawling campus on the outskirts of town has both teaching areas as well as residential blocks.
The university has several hundred students from different parts of Kenya, and the first bodies of some of those killed were flown to Nairobi late Thursday for families to collect on Friday, the start of the Easter weekend, a major holiday in the country.
A dawn until dusk curfew has been imposed on several northern and eastern Kenyan districts for two weeks.
Kenya has been hit by a wave of grenade and gun attacks, often blamed on sympathisers of the Shebab and sometimes aimed at police targets, since the army crossed into southern Somalia in 2011 to attack Islamist bases.
A series of foreign travel warnings in response to the threat have crippled Kenya's economically important tourism industry.
On Wednesday, just hours before the Garissa attack began, President Uhuru Kenyatta said Kenya "is as safe as any country in the world."
On Thursday, he offered his condolences to those killed but said security forces had made the "appropriate deployment to the affected area."
He also ordered the "urgent" enrolment of a planned 10,000 police recruit boost, warning Kenya had "suffered unnecessarily due to shortage of security personnel."
Kenya's government has been under fire since the Westgate attack. In June and July last year Shebab gunmen killed close to 100 people in a series of attacks on the town of Mpeketoni and nearby villages.
In November, the Shebab claimed responsibility for holding up a bus outside Mandera town, separating passengers according to religion and murdering 28 non-Muslims. Ten days later 36 non-Muslim quarry workers were also massacred in the area.